መነሻ ገጽ አዳማ ከተማ አስተያየት| አዳማ ከተማ 2-0 ወልዋሎ አ.ዩ.
አዳማ ከተማወልዋሎየአሰልጣኞች አስተያየትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አስተያየት| አዳማ ከተማ 2-0 ወልዋሎ አ.ዩ.

አጋራ
አጋራ

👉👉መደበኛ ልምምዶችን በአግባቡ የሰራንበት ሳምንት ይሄኛው ነበር።” (ደጉ ዱባም አዳማ ከተማ)

👉👉”በዳኛ አካባቢ ያያችሁትን ነገር መናገሩ ትርጉም ያለው አይመስለኝም።” (ኮማንደር ኪዳነ ሀፍተ – ወልዋሎ አ.ዩ.)

 

ም/አሰልጣኝ ደጉ ዱባም – አዳማ ከተማ

ስለ ጨዋታው

“እንዳያችሁት ጨዋታው ጥሩ ነው። ከመጀመሪያው ጀምሮ ለማጥቃት ነበር የተጫወትነው፤ የነበረው እንቅስቃሴ ጥሩ ነው።”

ስለ ተጋጣሚ ቡድን

“ወልዋሎ ጉዳትም አለበት፤ ተከታታይ ጨዋታ በመሸነፉ በሞራልም ረገድ ትንሽ መውረድ አለ። ከነበረበት ችግር አኳያ ዛሬ የነበረው እንቅስቃሴ መጥፎ አይባልም።”

ስለ አዳማ ተጫዋቾች ጥያቄ

“አሁን ሁሉም ነገር ጥሩ ነው፤ መስመር ይዟል፤ ግንኙነቱ አሁን የተሻለ ነው። መደበኛ ልምምዶችን በአግባቡ የሰራንበት ሳምንት ይሄኛው ነበር።”

ም/አሰልጣኝ ኮማንደር ኪዳነ ሀፍተ – ወልዋሎ አ.ዩ.

 

ስለ ጨዋታው

“ያው ጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ የተከላካያችን ጥንቃቄ አለማድረግ ዋጋ አስከፍሎናል። የገባው ጎል ያው በራሳችን ችግር ነው። በመጀመሪያው አጋማሽ 2-1 መሆን እንችል ነበር፤ የኛ ተጫዋቾች ግን ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል።”

ስለ ዳኛ

“በዳኛ አካባቢ ያያችሁትን ነገር መናገሩ ትርጉም ያለው አይመስለኝም። እናንተም ስላያችሁት መዘገብ ትችላላችሁ። በመጀመሪያው አጋማሽ ፍፁም ቅጣት ምት ሁለተኛው አጋማሽ የገባው ጎል ለናንተ ነው የምተወው። ሌላ የምለው ነገር የለኝም።”

ስለደጋፊው

“ደጋፊው ለኛ ጥሩ ክብር ነው የሰጠን። ማመስገን ነው የምንፈልገው። ከዛ ውጪ ያለው ግን እናንተ ባለሙያዎች ስለሆናቹ መዘገብ ትችላላችሁ።”

ስለ አቋም መውረድ

“የቋሚ ተሰላፊ የሆኑ 4 ወይም 5 ተጫዋቾች ጉዳት ላይ ነው ያሉት፤ እስካሁንም አልዳኑም።”

ስለ ቀጣይ እቅድ

“በቀጣይ ያሉብንን ችግሮች በሚገባ አስተካክለን ጥሩ ነገር እንሰራለን ብለን እናስባለን።”

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...