መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና አስተያየት| ሀድያ ሆሳዕና 0-1 ወላይታ ድቻ
ሀዲያ ሆሳዕናወላይታ ድቻየአሰልጣኞች አስተያየትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አስተያየት| ሀድያ ሆሳዕና 0-1 ወላይታ ድቻ

አጋራ
አጋራ

👉👉 አቅደን የመጣነው ነገር አሳክተናል (ደለለኝ ደቻሳ የወላይታ ድቻ ጊዚያዊ አሰልጣኝ)

👉👉እድል ከኛ ጋር አልነበረችም እንጂ በሁለተኛ አጋማሽ በርካታ አጋጣሚዎችን ፈጥረናል (ፀጋዩ ኪዳነማርያም የሀድያ ሆሳዕና አሰልጣኝ )

 

ቀሪ የ13ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም ሀዋሳ ላይ በተጣለበት ቅጣት ምክንያት ወላይታ ድቻን ያስተናገደው ሀድያ ሆሳዕና በወላይታ ድቻ 1-0 አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ አሰልጣኞቹ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።

አቅደን የመጣነው ነገር አሳክተናል (ደለለኝ ደቻሳ የወላይታ ድቻ ጊዚያዊ አሰልጣኝ)

ስለ ጨዋታው

“ጨዋታው እንዳያችሁት በጣም ከባድ ጨዋታ ነው። ሀድያ ሆሳዕና በስብስብ ስናየው በጣም ጥሩ ቡድን ነው በዛ ልክም ነው እኛ ተዘጋጅተን ነው የመጣነው። አቅደን የመጣነው ነገር አሳክተናል”።

በሁለተኛው ግማሽ መቀዛቀዛቸው

“ሀድያ ጥሩ ቡድን ነው። የኛ ተጫዋቾች ወጣቶች ናቸው። ሆኖም ግን እንደ ወላይታ ድቻ በመጀመሪያው አጋማሽ እና በሁለተኛው አጋማሽ ነጥብ ለመያዝ እየሰራን ስለሆነ አጨዋወታችን ይለያያል። በመጀመሪያው አጋማሽ ግብ ከማግባታችን በፊት እና ካገባን በኋላ ጥሩ ነበርን። ሁለተኛው አጋማሽ ግን የኋላ መስመራችንን ደፍነን በህብረት ለመጫወት ነው ሙከራ ያደረግነው”።

እድል ከኛ ጋር አልነበረችም እንጂ በሁለተኛ አጋማሽ በርካታ አጋጣሚዎችን ፈጥረናል (ፀጋዩ ኪዳነማርያም ሀድያ ሆሳዕና)

ስለጨዋታው

በጣም ጥቂት ቀናቶች ናቸው ከቡድኑ ጋር ቆይታ ያደረኩት። አራት ግዜ ብቻ ነው ልምምድ ያሰራሁት። ዛሬ ደግሞ ቡድናችን በውድድር ምን መልክ እንዳለው ለማየት ችያለው። በነበረው እንቅስቃሴ የመጀመሪያዎቹ ሀያ ደቂቃ የድቻ የበላይነት ነበር ማለት ይቻላል። በቀሩት ደቂቃዎች እና በሁለተኛው አጋማሽ በሙሉ ተጭነን መጫወት ችለናል። እድል ከኛ ጋር አልነበረችም እንጂ በሁለተኛ አጋማሽ በርካታ አጋጣሚዎችን ፈጥረናል። እንደ እንቅስቃሴ ድቻ በጥሩ መነቃቃት ያለ ቡድን ነው። እኛ ደግሞ ከሜዳችን ውጭም እንደመጫወታችን መጠን ጫናዎች አሉብን ተጫዋቾቼም ጫና ውስጥ ናቸው። የነጥቡም መራራቅ ተጨማሪ ጫና እንዳያሳድርብን እየሰራን ነው ያለነው። ይህ የመጀመሪያ ጨዋታየ ነው ብዙ ነገሮችን አሳይቶኛል። ቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አሉ ከነዚህ ስህተቶቻችን መነሻነት አድርገን እንሰራለን። በአብዛኛው ሁለተኛው ዙር ላይ አሻሽለን እንቀጥላለን።

ያገኙትን አጋጣሚ ወደ ግብ የመቀየር ችግር

ወደ ግብ ደርሰናል። የአጨራረስ ችግር ግን ነበረብን። እሱን ለማስተካከል ግዜ ይፈልጋል በቀጣይ እንፈታዋለን።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የ30ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች መናፍ ዐወል (አዳማ ከተማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...