መነሻ ገጽ ዜናዎች “አሰግድ ተስፋዬን”ያስታወሰው የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ዕውቅናና ሽልማት ሰጠ
ዜናዎችድሬዳዋ ከተማ

“አሰግድ ተስፋዬን”ያስታወሰው የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ዕውቅናና ሽልማት ሰጠ

አጋራ
አጋራ

የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ለድሬዳዋ ስፖርት ዕድገት አሰተዋጽኦ ለነበራቸው አካላት የምስክር ወረቀት ዕውቅናና ሽልማት አበርክቷል፡፡

የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ከድር ጁሃር የድሬዳዋ ስፖርት እንዲያድግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ሽልማት በሰጡበት ወቅት የስፖርት ኮሚሽኑ ያበረከተው የገንዘብ፡የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ዕውቅናና ሽልማት በሕይወት ላሉና ለስፖርት ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተው በህይወት ለሌሉትም ጭምር ነው ብለዋል፡፡

የድሬዳዋ ስፖርት ኮሚሽን ዕውቅናና ሽልማቱን በሰጠበት ወቅት ለስፖርቱ ዕድገት ከ1968 ዓ/ም እስካሁን ድረስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አሰልጣኞች፡ተጨዋቾች ዳኞችና አመራሮች እንዲሁም ለሌሎች ባለድርሻ አካላት መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

የድሬዳዋ ስፖርት ኮሚሽን ከድሬዳዋ ስፖርት ዕድገት ባሻገር ለሀገራችን ስፖርት ባለውለታ ናቸው በሚል እውቅናና ሽልማት ካበረከተላቸው መካከል ለቅዱስ ጊዬርጊስና ለምድር ባቡር እንዲሁም ለብሔራዊ ቡድን የተጫወተው ፍስሃ በጋሻው፡ለምድር ባቡር የተጫወተው ዘካሪያስ አሊ፡አሁን በህይወት የሌለው አሰግድ ተስፋየ እና የቀድሞ የከተማዋ ከንቲባ የነበሩት አቶ አበበ እሸቴ ይገኙበታል፡፡

በድንገተኛ ሞት የስፖርት ቤተሰቡን መሪር ሀዘን ውስጥ ከቶ ያለፈውን የቀድሞ የድሬዳዋ ኮካኮላ፡የቅዱስ ጊዬርጊስ፡የመድንና የቀድሞው ቡና ገበያ፡ያሁኑ ኢትዮጵያ ቡና በአጠቃላይ ለ4 ክለቦች ለ16 ዓመታት የተጫዎተው የ”አሰጌ ስፖርት አካዳሚ” መስራች የነበረውንና ሁሌም በኢትዮጵያውያን ልብ የማይዘነጋው አሰግድ ተስፈዬ በህይወት ባይኖርም ለስራዎቹ ስፖርት ኮሚሽኑ ዕውቅና መስጠቱ የሚያስመሰግን ነው፡፡

የስፖርት ኮሚሽኑ ለሽልማቱ ከ240 ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ዕውቅናና ሽልማት ሲሰጥ ለድሬዳዋ የስፖርት ዝናና ታዋቂነት የደከሙ አካላት ዛሬ ዕውቅና ሽልማት የተበረከተላቸው ብቻ ባለመሆናቸው በቀጣይ ሌሎችንም ዕውቅናና ሽልማት ለመስጠት ኮሚሽኑ እንደሚሰራ የተገለፀ ሲሆን ዛሬ የተሰጠው ዕውቅናና ሽልማት ለቀጣኝ ጊዜያት ትልቅ ተነሳሽነትን ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተነግሯል፡፡

በሽልማቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተው ሽልማቱን የሰጡት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ የዛሬው ዕውቅናና ሽልማቱ የቀድሞ የድሬዳዋን ገናና የስፖርት ስም ለመመለስ የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት እንደሚያግዝ ሲገልፁ የከተማ ከንቲባ ኢብራሂም ዑስማን በበኩላቸው ለተሸላሚዎች ዛሬ ሽልማቱን ያገኙት አካላት ለድሬዳዋ ስፖርት ትንሳኤ ያላቸውን ልምድ እንዲያካፍሉ ጥሪ መልዕክትም ጥሪም አስተላልፈዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...