መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ አለልኝ አዘነ ቅጣት ተላለፈበት
ሀዋሳ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አለልኝ አዘነ ቅጣት ተላለፈበት

አጋራ
አጋራ

 

የሀዋሳ ከተማው አማካይ አለልኝ አዘነ ዳኛን በቴስታ ለመምታት በማቃጣቱ በፌደሬሽኑ ተቀጥቷል።

በ14ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መርሀ ግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ትግራይ አቅንቶ መቐለ 70 እንደርታን ገጥሞ 5-1 መሸነፉ ይታወሳል። በዚህ ጨዋታ ተጨዋቹ ቢጫ ካርድ የሰጡትን ኢንተርናሽናል አርቢትር ብሩክ የማነብርሃንን በቴስታ ለመማታት ሲያቃጣው በቀይ ተሰናብቶ። የጨዋታ ታዛቢ ኮሚሽነር ያቀረቡትን ሪፖርት ተመልክቶ የፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን ኮሚቴ ። ተጫዋቹን ለአንድ አመት ከማንኛውም እግርኳሳዊ እንቅስቃሴ ያገደው ሲሆን 30ሺ ብር እንዲከፍልም ተወስኖበታል። ክፍያው በ7 ቀን ውስጥ ማስገባት አለበትም ተብሏል፡፡

ከአርባምንጭ ወደ ሀዋሳ ከተቀላቀለ በኋላ ድንቅ እንቅስቃሴን በማድረግ የወደፊቱ የሀገሪቱ ተስፋ የሚሆን ይህ ተጫዋች በእግር ኳስ እድገቱ ላይ መሰናክል ይሆንበታል ተብሎ ይጠበቃል። ተጫዋቹ የይግባኝ ደብዳቤ ማስገባቱም ተሰምቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...