ሽቶ ሚድያና ፕሮዳክሽን ከትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር የሚዘጋጀው ትግራይ ዋንጫ የዘንድሮ ዓመት ውድድሩን ከጥቅምት 30-ህዳር 9 በትግራይ ስታድየም ይካሄዳል።
ባሳለፍነው ዓመት አምስት የክልሉ ክለቦች(መቐለ 70 እንደርታ፣ወልዋሎ፣ደደቢት፣ስሑል ሽረ፣አክሱም ከተማ)፣አንድ ተጋባዥ ክለብ(ድሬዳዋ ከተማ)በማሳተፍ ለመጀመርያ ጊዜ ተካሂዶ በመቐለ 70 እንደርታ አሸናፊነት መጠናቀቁ ሚታወስ ነው።

ለሁለተኛ ጊዜ ሚካሄደው ትግራይ ዋንጫ በዘንድሮው ውድድር መቐለ 70 እንደርታ፣ስሑል ሽረ፣ደደቢት፣አክሱም ከተማ ና ሰሎዳ ዓድዋን ከክልሉ ሚያሳትፍ ሲሆን ተጋባዥ ክለቦችንም ሚያሳትፍ ይሆናል፤ጥሪ የቀረበላቸው ተጋባዥ ክለቦችም በሚቀጥሉት ቀናት መልሶቻቸውን ሚያሳውቁ ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ