ሁለተኛ ቀኑን የያዘው ትግራይ ዋንጫ የምድብ ሁለት መክፈቻ ጨዋታ የሆነውን የስሁል ሽረ ሰሎዳ ዓድዋ ጨዋታን አስተናግዶ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል።
ብዙ ሙከራዎች ባልታዩበት የመጀመርያ አጋማሽ ሰሎዳ ዓድዋ በአንጻሩ የተሻለ መንቀሳቀስ ቢችሉም ብዙ የግብ እድሎችን መፍጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።ስሁል ሽረ በወገናቸው መስመር ላይ ትኩረት አድርገው ከሁለቱም መስመር በሚነሱ ኳሶች እድሎችን ቢፈጥሩም የእለቱ ኮከብ የነበረው ሰንደይ ሮቲሚ አድኖባቸዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ከመጀመርያ አጋማሽ በተሻለ መልኩ ጠንካራ ፋክክር ታይቶበታል።በተለይ ስሑል ሽረ የተሻለ በመንቀሳቀስ ከቀኝ መስመር ተቀይሮ በገባው ዓወት ገብረሚካኤል እና ሳሊፍ ፎፎና አማካኝነት ያደረጉዋቸው ሙከራዎች የግቡ አግዳሚ ሲመልሳቸው አብዱልለጢፍ እና ሀብታሙ ያደረጉዋቸው ሙከራዎች ሰንደይ በሚገርም ሁኔታ አድኖባቸዋል።በዚህም የምድብ ሁለት መክፈቻ ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል።
የህዳር 2 ጨዋታዎች
7:30 | ወላይታ_ድቻ (ከ) ደደቢት
9:30 | መቐለ_70_እንደርታ ከ አክሱም ከተማ
አስተያየት ይስጡ