መነሻ ገጽ ዜናዎች ብሩክ አየለ ወደ ደቡብ ፓሊስ አምርቷል
ዜናዎችየዝውውር ዜናዎችደቡብ ፖሊስ

ብሩክ አየለ ወደ ደቡብ ፓሊስ አምርቷል

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ቆይታው ላይ ለሀዋሳ ከተማ ለሲዳማ ቡና ለኤሌክትሪክ እና ለወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ እንደዚሁም ደግሞ ለባህር ዳር እና በታዳጊ እና ወጣትነት ዕድሜው ደግሞ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ወጣት ቡድኖች ተጫውቶ ያሳለፈው የአማካይ ስፍራ ተጨዋቹ ብሩክ አየለ የፕሪሚየር ሊጉን ከዓመታት በኃላ ዘንድሮ በድጋሚ ለተቀላቀለው ደቡብ ፖሊስ ለመጫወት ለአንድ ዓመት ፊርማውን አኑሯል።

ባሳለፈው የእግር ኳስ ጨዋታ ዘመኑ የመሀል ሜዳው ላይ በሚያሳየው አበረታች ብቃት እና አጨዋወት የብዙዎችን ትኩረት ይስብ የነበረው ይኸው ተጨዋች ለደቡብ ፖሊስ መፈረሙ ከዚህ ቀደም በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ቡና አሰልጥኖት ካለፈው የቀድሞ አሰልጣኙ ዘላለም ሽፈራው /ሞውሪኖ/ ጋር ዳግም እንዲገናኝ ያስቻለው ሲሆን ተጨዋቹ በወልዋሎ ሳለ ደርሶበት ከነበረው ጉዳት ሙሉ ለሙሉ ድኖ በመምጣቱ ለአዲሱ ክለቡ በሙከራ ከታየ በኋላ እንደፈረመም ታውቋል።
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ዘንድሮ የተቀላቀለው ደቡብ ፖሊስ ከብሩክ ውጪ ሰሞኑን ሙልዓለም ረጋሳ እና አበባው ቡታቆን ማስፈረሙ ይታወሳል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...