የዝውውር መስኮቱ ዘግይተው ቢቀላቀሉም ንቁ ተሳትፎን በማድረግ ላይ የሚገኙት የጣና ሞጎዶቹ የአጥቂያቸውን ውል ማደሳቸው ተሰምቷል ::
በዝውውር መስኮቱ የአምስት ነባር ተጫዋቾችን ውል ያደሱት የጣና ሞገዶቹ ከደቂቃዎች በፊት የአጥቂያቸውን ወሰኑ ዓሊ ውል ማደሳቸው ተገልጿል።
በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የሚመሩት ባህር ዳር ከተማዎች እስካሁን የፍቅረሚካኤል ዓለሙ ፣ የዜናው ፈረደ ፣ አቤል ውዱ ፣ የደረጄ መንግስቱ እና የኃይለየሱስ ይታየውን ውል ለተጨማሪ 2 ዓመት ለማደስ መስማማታቸው ይታወሳል።
- ማሰታውቂያ -
ከደቂቃዎች በፊት የፊት መስመር አጥቂውን ወሰኑ ዓሊን ውል ለቀጣዩ ሁለት ዓመት ማደሳቸው ተሰምቷል ።