መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባህርዳር ከነማ እና ኮትዲቫራዊው አህመድ ቢን ዋታራ ሊለያዩ ነው
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ባህርዳር ከነማ እና ኮትዲቫራዊው አህመድ ቢን ዋታራ ሊለያዩ ነው

አጋራ
አጋራ

ኮትዲቫራዊው የመሃል አጥቂ አህመድ ቢን ዋታራ እና ባህርዳር ከነማ በስምምነት ሊለያዩ መሆኑ ታውቋል፡፡

የሊጉ አዲስ አዳጊው ባህርዳር ከነማ በኘሪምየር ሊጉ ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን በማሰብ በክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ካስፈረሟቸው የውጭ ሀገር ተጨዋቾች መሀከል ከመሀል አጥቂው ኮትዲቫራዊው አህመድ ቢን ዋታራ ጋር በስምምነት ለመለያየት ከጫፍ መድረሳቸውን ሀትሪክ ስፖርት አረጋግጣለች፡፡

አጥቂው አህመድ ቢን ዋታራ የሚጠበቅበትን ያህል ለክለቡ ግልጋሎት ባለመስጠቱ ከክለቡ ጋር የሚያቆየው ቀሪ ኮንትራት ውል ቢኖርም ክለቡ የአንድ ወር ደመወዝ እንክፈልህና በስምምነት እንለያይ የሚል ጥያቄ አቅርቧል፡፡

ተጨዋቹ በበኩሉ የአምስት ወር ደመወዝ ክፈሉኝና በስምምነት እንለያይ የሚል አማራጭ ሀሳብ ለክለቡ የበላይ ሀላፊዎች ጥያቄ አቅርቧል፡፡

በአንድ አመት ኮንትራት ውል በክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ባህርዳር ከነማን የተቀላቀለው ዋቴንጋ ብዙም የመሰለፍ ዕድል ሳያገኝ ለመጨረሻ ጊዜ ተሰልፎ የተጫዎተው የጣና ሞገዶቹ ከሜዳቸው ውጭ ሀዋሳ ላይ ከሲዳማ ቡና ጋር ነጥብ በተጋሩበት ጨዋታ ነበር፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...