መነሻ ገጽ ዜናዎች በ ኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር የሚካሄዱ ውድድሮች ቀናት ታውቀዋል
ዜናዎችየኢትዮጵያ ሴቶች ዋንጫየኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

በ ኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር የሚካሄዱ ውድድሮች ቀናት ታውቀዋል

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በ2011 ዓ.ም ከሚያካሂዳቸው አገር አቀፍ እና ኢንተርናሽናል ውድድሮች መካከል ከዚህ በታች የተገለፁትን ውድድሮች :-

v የኢትዮጵያ ሴቶች ኘሪሚየር ሊግ የ2011 ዓ.ም የሁለቱም ዲቪዚዮኖች ውድድር ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም የሚጀመር ይሆናል፡፡

v የኢትዮጵያ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በ2010 ዓ.ም የኘሪሚየር ሊግ ወንዶች አሸናፊ በሆነው በጅማ አባ ጅፋር ክለብ እና በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ አሸናፊ በሚሆነው ክለብ መካከል ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡

v የኢትዮጵያ ወንዶች ኘሪሚየር ሊግ የ2010 ዓ.ም የውድድር አፈፃፀም ግምገማ እና የ2011 ዓ.ም የዕጣ ማውጣት ሥነስርዓት መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል፡፡

v የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከኬንያ አቻው ጋር መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም በ10፡00 ሰዓት በባህር ዳር ስታዲየም እንደሚካሄድ የሚጠበቀው ጨዋታ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የስታዲየም ለውጥ እንደተደረገ የሚገለጸው መረጃ የተሳሳተ ሲሆን ውድድሩ በባህር ዳር ስታዲየም የሚከናወን ይሆናል ፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...