መነሻ ገጽ ዜናዎች በፋይናንስ ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ጅማ አባቡና አሰልጣኝ አንተነህ አበራ (ቲሾ)ን በሀላፊነት ሾሟል።
ዜናዎችየኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግጅማ አባቡና

በፋይናንስ ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ጅማ አባቡና አሰልጣኝ አንተነህ አበራ (ቲሾ)ን በሀላፊነት ሾሟል።

አጋራ
አጋራ

በ2009 የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ መልካም ግዜን ሳያሳልፍ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዶ በመወዳደር ላይ የሚገኘው ጅማ አባቡና አንጋፋውን አሰልጣኝ ግርማ ሐብተዮሐንስን ባሰናበተ ማግስት የቀድሞ የቡድኑን አሰልጣኝ አንተነህ አበራ (ቲሾ) ወደ ቡድኑ መመለሱ ተሰምቷል። 

ጅማ አባቡና በከፍተኛ ሊጉ  እያስመዘገብ ከሚገኘው ዝቅተኛ ውጤት በተጨማሪ በፋይናንሱ ረገድ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ለክለቡ ቅርበት ያላቸው ምንጮች  ለሀትሪክ ስፖርት ድህረ-ገፅ አስታውቀዋል። 

ቡድኑን ለመረከብ የወረቀት ስራዎች ብቻ እንደሚቀሩት የተናገረው አዲሱ አሰልጣኝ አንተነህ አበራ (ቲሾ ) “በቃል ደረጃ ተስማምተናል ሰኞ የውል ስምምነታችንን እንጨርሳለን ክለቡ በፋይናንስ ችግር ውስጥ ያለነው። ጅማ አባቡና ከመጀመሪያ የመሰረትኩት ቡድን ነው።  በነፃም ቢሆን እሰራለሁ ብዬ ተነጋግሬ  ተስማምቻለሁ። በቀጣይ ቡድኑን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማደረስ እሰራለሁ።”በማለት ለድህረ-ገፃችን አስተያየቱን ሊሰጥ ችሏል።

አሰልጣኝ አንተነህ አበራ (ቲሾ) ከዚህ ቀደም ጅማ አባቡና ፣ጅማ ከነማ(አባጅፋር)፣ከፋ ቡናን ማሰልጠኑ የሚታወስ ነው።

ጅማ አባቡና በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በምድብ-ለ  10ጨዋታዎችን አድርጎ በ15 ነጥብ በደረጃ ሰንጠረዡ 8ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...