መነሻ ገጽ ኢትዮጵያን በውጪ በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ወቅታዊ መረጃዎች !
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ወቅታዊ መረጃዎች !

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በተለያዩ አጋጣሚዎች እንዲሁም አሁን ላይ የቁርጥ ልጆች እንደሆኑ እያስመሰከሩ የሚገኙት ዑመድ ኡኩሪ እና ሽመልስ በቀለ በግብፅ ሊግ እንዲሁም ቢንያም በላይ በስዊድኑ ኡመያ ክለብ እየተጫወቱ ይገኛሉ ::

የመሐል ሜዳው ፈርጥ ሽመልስ በቀለ ከቀናት በፊት ከኢትዮጵያ ወደ ግብጽ ያመራ ሲሆን ከክለቡ አል መካሳ ጋር ይፋዊ ልምምድ መስራት ጀምሯል ። የግብፅ ሊጎች ከመጀመራቸው አስቀድሞ ክለቦች የወዳጅነት ጨዋታዎችን በማድረግ ላይ ሲገኙ የሽመልስ በቀለ ክለብ አል መካሳ በነገው እለት በቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ዲድዬ ጎሜስ በሚሰለጥነው እስማኤሊያ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል ።

ሌላኛው በግብፅ ሊግ እየተጫወተ የሚገኘው ዑመድ ኡክሪ በአስዋን ክለብ አንጸባራቂ ብቃቱን እያሳየ ቢቆይም ያለፉትን ወራት በከባድ ጉዳት ከሜዳ ተገሎ መቆየቱ ይታወቃል ። ከወደ ግብጽ በወጡ መረጃዎች ዑመድ ኡክሪ ከጉዳቱ በማገገም ቀለል ያሉ ልምምዶችን መስራት መጀመሩን ክለቡ አሳውቋል ። አስዋን ክለብ በዛሬው እለት ከ አረብ ኮንትራክተርስ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ሊያካሂድ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ለሌላ ጊዜ መዘዋወሩ ተሰምቷል ።

በአውሮፓዊቷ ስዊድን የመጀመሪያ የውድድር ዓመቱን እያሳለፈ የሚገኘው የመስመር ተጫዋቹ ቢንያም በላይ ከሰዓታት በፊት በተጠናቀቀው የሊጉ መርሀ ግብር ኡመያ ክለብ ሶስት ለ አንድ በሆነ ውጤት ሲያሸንፉ በመጀመሪያው አሰላለፍ በመካተት 89 ደቂቃዎችን በመጫወት አሳልፏል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...