በወልዲያና በመቐለ ከተማ እግር ኳስ ክለቦች መካከል ዛሬ ሊካሔድ የነበረው ግጥሚያ በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ወደ ሌላ ጊዜ መራዘሙን የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አስታወቀ።
የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ልባሴ አሊጋዝ ለሀትሪክ ስፖርት ድህረ ገፅ እንዳስታወቁት በወልዲያ ሼህ አላሙዲን ስታዲየም ሊካሔድ የነበረው ግጥሚያ ዛሬ ጠዋት በሁለቱ ክለቦች ደጋፊዎች መካከል በተነሳ ግጭት ምክንያት ሊካሔድ አልቻለም።
በግጭቱ ምክንያትም በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ለጊዜው ግምቱ ያልታወቀ የንብረት ጉዳት መድረሱን አስታውቀው የጸጥታ አካላት ባደረጉት ጥረት መረጋጋት መፈጠሩንም ተናግረዋል።
በሁለቱ እግር ኳስ ክለቦች መካከል ሊካሄድ የነበረው የ5ኛ ሳምንት ጨዋታም በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ሃላፊው ጨምረው አስታውቀዋል።
አስተያየት ይስጡ