መነሻ ገጽ ሉሲዎቹ ​በሴካፋ የሴቶች እግር ኳስ ውድድር የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የሁለተኛ ቀን ልምምዱን ትናንትና በሩዋንዳ አድርጓል
ሉሲዎቹሴካፋዜናዎች

​በሴካፋ የሴቶች እግር ኳስ ውድድር የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የሁለተኛ ቀን ልምምዱን ትናንትና በሩዋንዳ አድርጓል

አጋራ
አጋራ

በሩዋንዳ የሚካሄደው ሶስተኛው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ (ሴካፋ) የሴቶች እግር ኳስ ውድድር ትናንት ተጀምሯል ።
በአገሪቷ ርዕሰ መዲና ኪጋሊ በሚካሄደው ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ አዘጋጇ ሩዋንዳ ፣ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያና ኬንያ ይሳተፋሉ።

በውድድሩ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 20 ተጫዋቾችና ሌሎች 10 ልዑካንን በመያዝ ከትናንት ወዲያ ወደ ሩዋንዳ በማምራት ማምሻውን የአገሪቷ ርዕሰ መዲና ኪጋሊ መድረሱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።

በሰላም ዘርአይ አሰልጣኝነት የሚመራው ብሔራዊ ቡድኑ ትናንትና የሁለተኛ ቀን ልምምዱን ማድረጉም ተገልጿል።

ሉሲዎቹ ከሐምሌ 1 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ለውድድሩ ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን የውድድሩን የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ቅዳሜ ሐምሌ 14 ቀን 2010 ዓ.ም ከኡጋንዳ ጋር በሩዋንዳ ብሔራዊ ስታዲየም ከቀኑ 8 ሰዓት ከኡጋንዳ አቻው ጋር ያደርጋል።

በአጠቃላይ አምስቱ አገራት እርስ በእርስ በሚያደርጓቸው ጨዋታዎች የተሻለ ነጥብ ያስመዘገበ ቡድን የውድድሩ አሸናፊ እንደሚሆን የምስራቅና የመካከለኛው አፍሪካ የክለቦች ማህበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) አስታውቋል።

የሴካፋ የሴቶች እግር ኳስ ውድድር እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2010 ዓ.ም ይቆያል።

የምስራቅና የመካከለኛው አፍሪካ የክለቦች ማህበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ውድድሩን ለማዘጋጀት የሚያስፈልገውን ወጪ በተቀመጠለት ጊዜ ለአዘጋጇ ሩዋንዳ ባለመላኩ ውድድሩ ከግንቦት ወር 2010 ዓ.ም ጀምሮ በተደጋጋሚ  ሲራዘም ቆይቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...