ቅ/ጊዮርጊስ ጋናዊውን የ25 ዓመት አጥቂ አርተር ሪቻርድን በ2 ዓመት የውል ስምምነት አስፈርመዋል።
አዲስ ፈራሚው የፈረሰኞቹ አጥቂ አርተር ሪቻርድ ከአሳዳጊው ክለብ ዋ ኦልስታር ወደ ባህሬን ሊያመራ እንደነበርና ለፈረሰኞቹ ቅድሚያ ሰጥቶ ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ አማራ ስፖርት አረጋግጣለች፡፡
ፈረሰኞቹ በዘንድሮ የውድድር ዓመት የመጡትን አሌክስ ኦሮትማልና ካሲሙ ታይተስ ያልተሳካ የውድድር ጊዜ በማሳለፋቸው በስምምነት ከሳምንት በፊት ማሰናበታቸው ይታወሳል፡፡
ለዚህም ምትክ ይሆን ዘንድ በዛሬው ዕለት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ጋናዊውን አርተር ሪቻርድ በሁለት ዓመት ኮንትራት ውል አስፈርመዋል። ተጫዋቹ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2ኛ ዙር ሲጀምር ሜዳ ላይ የምንመለከተው ይሆናል።
ተጨዋቹ የፈረሰኞቹን ቤት ግብ የማስቆጠር ችግር በሁለተኛው ዙር የሊግ ውድድር እንደሚቀርፍ እምነት ተጥሎበታል፡፡
Photo credit – saint georg official page
አስተያየት ይስጡ