መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ |ወልዋሎ ከ ሀዋሳ ከተማ
ሀዋሳ ከተማቅድመ ዳሰሳወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ |ወልዋሎ ከ ሀዋሳ ከተማ

አጋራ
አጋራ

ወልዋሎ ከ ሀዋሳ ከተማ
የጨዋታ ቀን: ቅዳሜ ታህሳስ 25/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር:
ቦታ: ትግራይ ስታድየም

ባሳለፍነው ሳምንት ደርቢ ጨዋታዎችን አካሂደው ሽንፈት ያስተናገዱት ወልዋሎ እና ሃዋሳ ከተማ ነገ በትግራይ ስታድየም ሚገናኙ ይሆናል።የሊጉ መሪ የሆኑት ወልዋሎዎች መሪነታቸውን ለማስጠበቅ ሀይቆቹ በበኩላቸው ከመሪዎቹ ተርታ ለመሰለፍ ጠንካራ ፋክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ቢጫ ለባሾቹ ወልዋሎዎች ከመቐለ 70 እንደርታ ጋር በነበረው ጨዋታ ጉዳት ያስተናገደው አይናለም ሀይሉ፣በ3ተኛው ሳምንት ከስሁል ሽረ ጋር በነበረው ጨዋታ ጉዳት ያስተናገደው አቼምፖንግ አሞስ፣ለዮውሃንስ ሳህሌ አጨዋወት አመቺ እንደሆነ ሚነገርለት ካርሎስ ዳምጠው በጉዳት ምክንያት ከነገው ጨዋታ ውጪ ሲሆኑ፤በደርቢው ጨዋታ በሁለት ቢጫ ከሜዳ የተሰናበተው ግብ ጠባቂው አብዱላዚዝ ኬይታ በቅጣት ሃይቆቹን ማይገጥም ይሆናል።በሃዋሳዎች በኩል ወጣት ተከላካያቸውን መሳይ ፖውሎስን መልሰው ሲያገኙ ቸርነት አውሽ በጉዳት አያሰልፋም።

መነሻቸው ከሁለቱን መስመሮች ባደረጉ ተሻሚ ኳሶች እድሎችን ለመፍጠር ሚሞክሩት ወልዋሎዎች በነገውም ጨዋታ ተመሳሳይ አቀራረብ ይዘው ሊገቡ እንደሚችሉ ይገመታል።በሊጉ የመጀመርያ ሥስት ጨዋታዎች ላይ ድንቅ ብቃቱን ያሳየው ወጣቱ አጥቂ ሰመረ ሀፍታይ በነገው ጨዋታ ከኢታሙና ኩሜይኒ እና ጁንያንስ ናንጂቦ ጋር ሚኖራቸው ጥምረት የወልዋሎ ውጤት ማማር ላይ ከፍተኛ ድርሻ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎችን የተሸነፋት ሃዋሳዎች በበኩላቸው ከሜዳቸው ውጪ እንደመጫወታቸው ጥንቃቄ ላይ መሰረት ያደረገ በወጣቶቹ አጥቂዎች ብሩክ በየነ እና መስፍን ታፈሰ ላይ ትኩረት ያደርገ አጨዋወትን ሊከተሉ እንደሚችሉ ይገመታል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...