መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ
ሀዋሳ ከተማቅድመ ዳሰሳኢትዮጵያ ቡናየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት የመጨረሻ አንድ ጨዋታ ነገ ይደረጋል።

የ2012 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት 7ጨዋታዎች ዛሬ (ቅዳሜ) የተደረጉ ሲሆን የመጨረሻ አንድ ጨዋታ ደግሞ ነገ (እሁድ) የሚደረግ ይሆናል።
ሁለት በተለያየ አቋም ላይ በሚገኙት ቡድኖች መካከል የሚደረገው ይህ ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም ኢትዮጵያ ቡናን እና ከሀዋሳ ከተማ ጋር የሚያገናኝ ይሆናል።

በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሊጉ ጥሩ ግስጋሴ ማድረግ ያልቻለው እና እስካሁን በሊጉ ድል ማስመዝገብ ያልቻለው ኢትዮጵያ ቡና በኢ/ር ካሳዬ አራጌ እየተመራ የመጀመሪያ ሶስት ነጥቡን ለማስመዝገብ እና ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት እንዲሁም በጥሩ አቋም ላይ የሚገኘው ሀዋሳ ከተማ ደግሞ ያለመሸነፍ ሪከርዱን ለማስጠበቅ እና ከመሪዎቹ ተርታ ላለመራቅ የሚያደርጉት ጨዋታ ስለሆነ ከባድ ፉክክር ይስተዋልበታል ተብሎ ይጠበቃል።

በ3ኛው ሳምንት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ወደ መቐለ ተጉዞ ከመቐለ ከተማ ጋር 1-1 በሆነ አቻ ውጤት መመለስ ሲችል ሀዋሳ ከተማ በአንፃሩ በብሩክ በየነ ብቸኛ ግብ ባህርዳር ከተማን በማሸነፍ የሊጉን መሪ ወልዋሎን በቅርብ ርቀት መከተል ጀምሯል። ውጤቶቹም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና በ2ነጥቦች 13ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሀዋሳ ከተማ ደግሞ በ7 ነጥቦች 2ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል። የነገውን የሁለቱን ቡድኖች ጨዋታ ኢንተርናሽናል አርቢትር አማኑኤል ኃ/ስላሴ የሚመሩት ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የ30ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች መናፍ ዐወል (አዳማ ከተማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ በመድን ሲሸነፍ የጣና ሞገዶች እና ሰጎኖቹ ድል ቀንቷቸዋል

በሊጉ የሳምንቱ የማሳረጊያ ቀናት ሦስት ጨዋታዎች በኢትዮጵያ መድን ፣ ባህርዳር ከተማ እና...