መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ባህርዳር ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ እና ወልቂጤ ከተማን ከሰበታ ከተማ
ሰበታ ከተማቅድመ ዳሰሳባህርዳር ከተማወልቂጤ ከተማዜናዎችድሬዳዋ ከተማ

ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ባህርዳር ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ እና ወልቂጤ ከተማን ከሰበታ ከተማ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት 7ጨዋታዎች ነገ ይደረጋሉ።

የ2012 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት 8 ጨዋታዎች በሳምንቱ መጨረሻ የሚደረጉ ሲሆን 7ጨዋታዎች ነገ (ቅዳሜ) እንዲሁም 1ጨዋታ ደግሞ ከነገ በስትያ (እሁድ) የሚደረግ ይሆናል። ከነዚህ መካከል 6ቱ ጨዋታዎች ክልል ላይ ሲደረጉ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ላይ ይደረጋሉ።

ቅዳሜ ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል ባህርዳር ላይ ባህርዳር ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ 9:00 ላይ የሚጀምር ይሆናል። ሁለቱ ቡድኖች የዘንድሮውን ውድድር በመልካም ሁኔታ መጀመር ተስኗቸው 4ኛ ሳምንት ውድድር ላይ ደርሰዋል። በ3ኛው ሳምንት ባህርዳር ከተማ ወደ ሀዋሳ አቅንቶ በሀዋሳ ከተማ 1-0 ሽንፈት ያስተናገደ ሲሆን ድሬዳዋ ከተማ በአንፃሩ በሪችሞንድ ኦዶንጎ ግብ ታጅቦ አዲስ አዳጊውን ሀድያ ሆሳዕናን 1-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ሁለቱ ክለቦች በደረጃ ሰንጠረዡ በአንድ ነጥብ ተበላልጠው ባህርዳር ከተማ በ4 ነጥቦች 9ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ድሬድዋ ከተማ ደግሞ በ3ነጥቦች 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የሁለቱን ቡድኖች ጨዋታ ኢንተርናሽናል አርቢትር ሊዲያ ታፈሰ የምትመራው ይሆናል።

በሌላ የሊጉ የ9 ሰዓት ጨዋታ ሁለቱን አዲስ አዳጊዎቹን ወልቂጤ ከተማን ከሰበታ ከተማ ጋር የሚያገናኘው ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል። በኢንተርናሽናል አርቢትር ብሩክ የማነብርሃን የሚመራው ይህ ጨዋታ ለሁለቱም ቡድኖች በጣም ወሳኝ ነው። ጨዋታውን ወሳኝ የሚያደርገው ነገር ወልቂጤ ከተማ በ3ኛው ሳምንት ያገኘውን ድል ለማስቀጠል ሰበታ ከተማ ደግሞ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርገው ጨዋታ መሆኑ ነው። ሰበታ ከተማ በ3ኛው ሳምንት አዳማ ከተማን አስተናግዶ አቻ ሲለያይ ወልቂጤ ከተማ ደግሞ በክለቡ ታሪክ በፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ 3ነጥቦችን ፋሲል ከተማን በማሸነፍ ማግኘት ችሏል። ሁለቱ ቡድኖች ባደረጓቸው ሶስት ጨዋታዎች ሰበታ ከተማ በ1ነጥብ የሊጉ ግርጌ ላይ ሲገኝ ወልቂጤ ከተማ ደግሞ በ4ነጥቦች 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...