መነሻ ገጽ ስሁል ሽረ ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ስሁል ሽረ ከ አዳማ ከተማ
ስሁል ሽረቅድመ ዳሰሳአዳማ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ስሁል ሽረ ከ አዳማ ከተማ

አጋራ
አጋራ

5ተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቅዳሜ በሚካሄዱ 6 ጨዋታዎች ቀጥሎ ይውላል።በትግራይ ስታድየም ሚካሄደው የስሁል ሽረ ና የአዳማ ከተማ ጨዋታን እንዴት ሊመስል እንደሚችል በዚህ መልኩ አቅርበንላችኃል።

ባሳለፍነው ሳምንት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ነጥብ ተጋርተው የተመለሱት ስሁል ሽረዎች ነገ በሜዳቸው በሚያደርጉት ጨዋታ ተከላካያቸው ዮናስ ግርማይ በቅጣት ከማጣታቸው በስተቀር ሙሉ ቡድናቸውን ይዘው ወደ ሜዳ ይገባሉ።በ4ተኛው ሳምንት ከደሞዝ በወቅቱ አለመከፈል ጋር ተያይዞ ከቡድኑ ጋር ወደ አዲስ አበባ ያልተጓዙት አክሊሉ ዋለልኝ፣ያሰር ሙገርዋ፣ሳሊፍ ፎፎና ና ዲድዬ ሌብሪ ወደ ቡድኑ የተመለሱ ሲሆን በጉዳት ፈረሰኞቹን ያልገጠመው ምንተስኖት አሎም ከጉዳቱ አገግሞ ለነገው ጨዋታ ዝግጁ ሆኗል።ከመስመር በሚነሱ ኳሶች እድሎችን ለመፍጠር ሚሞክሩት ስሁል ሽረዎች እስካሁን በተካሄዱት 5 ጨዋታዎች ሁለት ግቦችን ብቻ ያስተናገደውን የአዳማ ተከላካይ ክፍልን ሰብሮ ለመግባት መሀል ላይ የአጥቂ አማካዮቻቸውን ቁጥር አብዝተው ሊገቡ አንደሚችሉ ይገመታል።

አዳማዎች በበኩላቸው በክረምቱ ያስፈረሙት አጥቂያቸው ሚኪኤለ ጆርጅን ከጉዳት መልስ ሲያገኙ የመሀል አማካዮቻቸው አመለ ሚልክያስ እና አማኑኤል ጎበና ግልጋሎት ማያገኙ ይሆናል።ፊት ላይ በሚያሰልፏቸው ዳዋ ሆቴሳ፣በረከት ደስታ እና ቡልቻ ሹራ ጥምረት ላይ ጥገኛ የሆነው የአዳማ ከተማ የማጥቃት እንቅስቃሴ ደካማ ተከላካይ ክፍልን ለያዘው ስሁል ሽረ ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...