መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና ቅድመ ዳሰሳ | ወልዋሎ አዲግራት.ዮ ከ ሀድያ ሆሳእና
ሀዲያ ሆሳዕናቅድመ ዳሰሳወልዋሎየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ዳሰሳ | ወልዋሎ አዲግራት.ዮ ከ ሀድያ ሆሳእና

አጋራ
አጋራ

8ተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዕለተ እሁድ ላይ ሰባት ጨዋታዎችን ያካሂዳል።በትግራይ ስታድየም ላይ ሚካሄደው የወልዋሎ ና ሀድያ ሆሳእና ጨዋታን ከጨዋታው በፊት በዚህ መልኩ ዳስሰነዋል።

ወልዋሎ አዲግራት ከ ሀድያ ሆሳእና
የጨዋታ ቀን: እሁድ ጥሪ 2/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር: ኢንተርናሽናል አርቢትር ሊድያ ታፈሰ
ቦታ: ትግራይ ስታድየም

ባሳለፍነው ሳምንት ከተከታታይ ነጥብ ማጣት በኃላ ማሸነፍ የቻሉት ወልዋሎዎች መሪነታቸውን ለማስጠበቅ የሊጉ ጊርጌ ላይ ሚገኘውን ሀድያ ሆሳእናን ማሸነፍ ግድ ይለዋል።ባለፋት ጨዋታዎች ላይ ወሳኝ ተጨዋቾቹን በጉዳት ያጣው ወልዋሎ በነገው ጨዋታም በተመሳሳይ አይናለም ሀይሉ፣አሞስ አቼምፖንግ እና ካርሎስ ዳምጠውን ማያሰልፍ ይሆናል።

ድሬዳዋን ባሸነፋበት ጨዋታ ተፈጥሮአዊ የመሀል ሜዳ ተጨዋቾችን ይዘው የገቡት ቢጫ ለባሾቹ ነገም የተጋጣሚያቸውን የመሀል ሜዳ ጥንካሬ በግምት በማስገባት ተመሳሳይ አቀራረብ ይዘው ሊገቡ እንደሚችሉ ይገመታል።ፊት ላይ ጥሩ ጥምረት እየፈጠሩ ሚገኙት ናሚብያውያኑ ኢታሙና ኩሜይኒ ና ጁንያንስ ናጋንጂቦ ከሜዳው ውጪ ወደ ኃላ ሚያፈገፍገውን የሀድያን ተከላካይ ክፍል ማስከፈት ላይ ከባድ ስራ ይጠብቃቸዋል።በተለይ ቡድኑ ላይ ያለው የፈጣሪ ተጨዋች እጥረት አጥቂዎቹን ለተጨማሪ ጥረት ሲያጋልጣቸው ይታያል።

የሊጉ የመጀመርያ ድላቸውን ሲዳማ ቡና ላይ ያስመዘገቡት ሀድያ ሆሳእናዎች የነገው ጨዋታ ከሜዳቸው ውጪ እንደመሆኑ ወደ ኃላ ተስበው ጥንቃቄ ላይ መሰረት ያደርገ አቀራረብን ይጠቀማሉ ተብሎ ይጠበቃል።አምስት ነጥቦችን ሰብስበው የሊጉ መጨረሻ ደረጃን ይዘው ሚገኙት ሀድያዎች ለነገው ጨዋታ የመሐመድ ናስርና ኢዮኤል ሳሙኤልን ግልጋሎትን በጉዳት ምክንያትማያገኙ ይሆናል።

3-5-2(ኳስ ሲነጠቁ ወደ 5-3-2 ሚቀየር) የጨዋታ ስልትን ተመራጭ ሚያደርጉት ሀድያዎች ከመስመር ና ከመሀል በሚንሱ ኳሶች በመልሶ ማጥቃት እድሎችን ለመፍጠር ሊሞክሩ ይችላሉ።በተለይ የፊት አጥቂዎቹ ቢስማርክ አፖንግ ና ቢስማርክ አፒያ የዚህ እንቅስቃሴ ቁልፍ ተጨዋቾች ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል።በተጨማሪ መሀል ሜዳ ላይ ሚሰለፋት አፈወርቅ ሀይሉ ና ይሁን እንደሻው ቡድናቸው ከመከላከል ወደ ማጥቃት በሚሸጋገርበት ወቅት ሚና ትልቁን ቦታ ሚይዝ ይሆናል።ከሜዳቸው ውጪ መጥፎ ክብረ ወሰን ያላቸው ሀድያዎች መጥፎ አጀማመራቸውን ለማስተካከል ከዚህ ጨዋታ ነጥብ ይዞ መውጣት ግድ ያላቸዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...