መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና ቅድመ ዳሰሳ | ሲዳማ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ
ሲዳማ ቡናቅድመ ዳሰሳባህርዳር ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ዳሰሳ | ሲዳማ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በሳምንቱ መጨረሻ የሚደረጉ ሲሆን ዛሬ (ቅዳሜ) አንድ ጨዋታ የተደረገ ሲሆን ነገ (እሁድ) ደግሞ ሰባት ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል። በነገው እለት ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል ሲዳማ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ የሚያደርጉትን ጨዋታ ለእናንተ እንዲስማማ አድርገን እንደሚከተለው ዳሰነዋል። መልካም ንባብ።

ጨዋታ: ሲዳማ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ
የጨዋታ ቀን: እሁድ ጥር 03/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር: ፌደራል አርቢትር ወልዴ ንዳው
የጨዋታ ቦታ: ይርጋለም ስታዲየም

የስምንተኛው ሳምንት ከሚያተናግዳቸው ሌላኛው ተጠባቂ መርሀ ግብር ይህ ዋነኛው ነው።
ሲዳማ ቡና በአስፈሪው የፊት መስመሩ ማለት በአዲስ ግደይ ፤ ሀብታሙ ገዛኸኝ እና ይገዙ ቦጋለ እየተመሩ ጥሩ ጅማሮን ማድረግ ቢችሉም ባለፉት የሊጉ ጨዋታዎች ላይ በተከታታይ ነጥብ እየጣሉ ይገኛሉ።
ሁለቱ ቡድኖች በስምንተኛው ሳምንት ሲገናኙ በሁለት ነጠቦች ብቻ ተራርቀው ነው ፡፡ በተለይም ደግሞ በሊጉ የነጥብ መቀራረበች ይበልጥኑ ለሊጉ ድምቀት ሰጥቶት ታይቷል ፡፡
ባህር ዳር ከተማ በአዲሱ አሰልጣኛቸው ፋል ተካልኝ እየተመሩ በሊጉ ጥሩ ጉዞን እያረጉ ይገኛሉ ፡፡ በተለይም በሁለቱ ቡድኖች መካከል ከሚጠበቀው ብረቱ ፉክክር አንዱ የሁለቱም ቡድኖች የፊት መስምር ጥንካሬ አንደኛው ነው ፡፡
ለተመልካች አዝናኝ እንደሚሆን በሚጠበቀው በዚህ መርሀ ግብር ባለሜዳዎቹ ሲዳማ ቡናዎች ድል የሚቀናቸው ከሆነ በአስራ ሁለት ነጥብ በሊጉ ሶስተኛ ላይ የሚያስቀመጣቸውን ውጤት የሌሎችን ቡድኖች ውጤት ጠብቀው የሚቀመጡ ይሆናል ፡፡
በሌላ በኩል ባህርዳር ከተማዎች ድልን የሚጎናፀፉ ከሆነ በአስራ አራት ነጥብ የሌሎች ክለቦችን ነጥብ መጣል ጠብቀው የሊጉ መሪ እስከ መሆን የሚያስችላቸውን ደረጃ ያገኛሉ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...