መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ ቅድመ ደሰሳ | መቐለ 70 እንደርታ ከ አዳማ ከተማ
መቐለ 70 እንደርታቅድመ ዳሰሳአዳማ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ደሰሳ | መቐለ 70 እንደርታ ከ አዳማ ከተማ

አጋራ
አጋራ

መቐለ 70 እንደርታ ከ አዳማ ከተማ
የጨዋታ ቀን: ረቡዕ ታህሳስ 29/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር: ኢንተርናሽናል አርቢትር ቴዎድሮስ ምትኩ
ቦታ: ትግራይ ስታድየም

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 7ተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከልደት በዓል ማግስት ቀጥሎ ሰባት ጨዋታዎችን ያስተናግዳል።መቐለ ላይ የውድድሩ የአምናው ሻምፒዮን መቐለ 70 እንደርታ አደማ ከተማን ሚያስተናግድ ይሆናል።ከቀኑ 9 ሰዐት ሲል ሚጀምረውን ጨዋታ በዚህ መልኩ ዳስሰነዋል።

ባሳለፍነው ሳምንት በቅዱስ ጊዮርጊስ ሽንፈት የደረሰባቸው መቐለ 70 እንደርታዎች አንጋፋ ተጨዋቻቸውን ሚኪኤለ ደስታን አሁንም በጉዳት ማያሰልፋ ይሆናል።ፈረሰኞቹን በገጠሙበት ዕለት ደካማ እንቅስቃሴን ያሳዩት ምዐም አናብስቶቹ ቀዋሚ 11 ተሰላፊዎች ላይ ለውጦችን ሊያደርጉ እንደሚችሉ ይገመታል።በሜዳቸው በሚያደርጉዋቸው ጨዋታዎች ላይ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ወስደው መጫወትን ተመራጭ ሚያደርጉት መቐለዎች በዛሬው ጨዋታም ተመሳሳይ አጨዋወትን ይዘው ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በያዝነው ውድድር አመት ምንም ሽንፈትን ያላስተናገዱት አዳማዎች በበኩላቸው ሚካኤል ጆርጅ እና ብሩክ ቃልቦሬን በጉዳት ማያሰልፋ ይሆናል።ባሳላፍነው ሳምንት ከጅማ አባጅፋር ጋር ነጥብ የተጋሩት አዳማዎች በአብዛኛው መከላከል ላይ ትኩረት አድርገው በመልሶ ማጥቃት እድሎችን ለማግኘት ይሞክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።በተለይ ፊት ላይ ሚያሰልፍዋቸው ፈጣን ተጨዋቾች አጨዋወቱን መተግበር ላይ ከባድ ሀላፊነት ሊሰጣቸው እንደሚችል ይገመታል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...