- ሳምንታዊ ባለቀለም የስፖርት ጋዜጣ የሆነችው ተወዳጇ ሀትሪክ
ስፖርት ጋዜጣ እንደተለመደው ሁሉ ነገም ማክሰኞ ህዳር
26/2010 ዓ.ም በማለዳው በእጅዎ ልትገባ መሰናዶዋን
አጠናቅቃለች፡፡
ለመሆኑ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ይሆን?
-ከሀገር ውስጥ፡- በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 6ኛ ሳምንት እሁድ 10:00 ሰዓት በሸገር ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደረጉት ጨዋታ ከወዲሁ አጓጊ ሆኖል፡፡ የሁለቱ ክለብ ተጨዋቾች በረከት ይስሀቅ፣አክሊሉ ዋለልኝ፣ ሙሉአለም መስፍን (ዲኮ)፣አብዱልከሪም መሀመድ(ተርሚኔተር)፣ ስለ ደርቢው ጨዋታ ምን አሉ ነገ ማለዳ ይጠብቁን!
ከባህር ማዶ፡- አርሰናሎች በሳምንቱ መጨረሻ በማንቸስተር ዮናይትድ የደረሰባቸውን አሳዛኝ ሽንፈት አስመለክቶ ተጫዋቾች ምን ይላሉ ዳሰነዋል? እናም ሌሎች ያልተሰሙ አዳዲስና ትኩስ
ዘገባዎችን ነገ ማለዳ ይዛ እጅዎ ትገባለች፡፡
በርካታ አንባቢዎቻችን ባቀረባችሁልን ተደጋጋሚ ጥያቄ መሰረት
ሀትሪክን በሳምንት ሁለት ቀን በቅርቡ ይዘን እንቀርባለንና
ጠብቁን፡፡ ተጨማሪና ትኩስ መረጃዎችን በርካታ ተከታታዮች
ባሉት hatricksport.com ድህረ-ገፃችን ይጎብኙን፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል፡፡
መልካም ንባብ

አስተያየት ይስጡ