መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና ሲዳማ ቡና የተጫዋቹን ውል አራዝሟል !
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ሲዳማ ቡና የተጫዋቹን ውል አራዝሟል !

አጋራ
አጋራ

 

የተጫዋቾቻቸውን ውል በማራዘም ላይ የሚገኙት ሲዳማ ቡናዎች በሊጉ ልምድ አላቸው ከሚባሉ የውጭ ሀገር የተከላካይ ስፍራ ተጫዋቾች አንዱ የሆነውን የሰንደይ ሙቱኩን ኮንትራት አራዝሟል ።

ኬንያዊው የመሐል ተከላካይ ለቀጣይ ሁለት ዓመት በሲዳማ ቡና ቤት የሚያቆየውን ውል ከጥቂት ሰዓታት በፊት መፈራረሙ ይፋ ሆኗል ።

ሀትሪክ ስፖርት ከተጫዋቹ ጋር ከፊርማ ስነ ስርዓቱ በኋላ ቆይታ ስታደርግ ” ሁለተኛ ቤቴ በሆነው ክለብ ሲዳማ ቡና ጋር ውሌን በማራዘሜ ደስተኛ ነኝ ። የአሰልጣኙን የአጨዋወት ዘይቤ ለመረዳት ችያለው በቀጣይ ዓመት ከሲዳማ ቡና ጋር በአፍሪካ የውድድር መድረኮች ላይ ተሳተፊ ለመሆን ጠንክሬ እሰራለሁ ” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል ።

ሰንደይ ሙቱኩ ከሌሎች ክለቦች በተለይም በባህር ዳር ከተማ በጥብቅ ቢፈለግም በሲዳማ ቡና ቤት ውሉን አራዝሟል ::

ከሰንደይ ሙቱኩ በተጨማሪም ሲዳማ ቡናዎች የብርሀኑ አሻሞን ውል ማራዘም ሲችሉ በመጪው ቀናት የነባር ተጫዋቾችን ውል ጨምሮ አዳዲስ ተጫዋቾች ቡድኑን እንደሚቀላቀሉ ሀትሪክ ስፖርት ለማወቅ ችላለች ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...