መነሻ ገጽ ሪፖርት ሪፖርት | ሰበታ ከተማ በሜዳው ጅማ አባጅፋርን አሸንፏል
ሪፖርትሰበታ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግጅማ አባጅፋር

ሪፖርት | ሰበታ ከተማ በሜዳው ጅማ አባጅፋርን አሸንፏል

አጋራ
አጋራ

በተቀዛቀዘ የደጋፊዎች ድባብ በተጀመረው የሁለቱ ቡድኖች የስምንተኛ ሳምንት መርሀ ግብር መስኡድ መሀመድ የቀድሞው ክለቡን ለመጀመሪያ ጊዜ ገጠሟል ::

ሰበታዎች አጥቅተው በመጫወት የመጀመሪያውን አስር ደቂቃዎች ወደ ጅማ የግብ ክልል ሲደርሱ የተስተዋሉት ሰበታዎች በግራ መስመር ወንዲፍራው ጌታሁን ወደ ሳጥን ይዞ የገባውን ኳስ በጅማ ተከላካዮች ተጠልፎ ፍፁም ቅጣት ምት ማግኘት ችለዋል ::

የተገኘውን ፍፁም ቅጣት ፍፁም ገብረ ማርያም ሲያስቆጥር ባለፉት አራት የሊጉ ጨዋታዎች ላይ ያስቆጠራቸውን የጎል መጠን ወደ አራት ከፍ ማድረግ ችሏል ::

ከግቡ መቆጠር በኋላ መሀል ሜዳውን በቁጥር በመብለጥ ኳስን ይዘው መጫወት የፈለጉት ሰበታዎች አልፎ አልፎ የግብ ሙከራዎችን ሲያደርጉ ከግራ መስመር ተሻምቶ ባኑ ዲያዋራ የሞከራት ኳስ የምታስቆጭ አጋጣሚ ነበረች ::

ከጎሉ መቆጠር በኋላ ጅማ አባ ጅፋሮች የጎል እድሎችን ለመፍጠር ቢሞክሩም የተሳካ ሙከራን ማድረግ ተስኗቸው ተስተውሏል ::

በተለይም በመልሶ ማጥቃት ያገኙትን ኳስ ጀሚል ያቆብ ለመሀመድ ያኩቡ አሻግሮሎት ሳይጠቀምበት የቀረው አጋጣሚ በጅማዎች በኩል የሚጠቀስ ሙከራ ነበር ::

በሰበታ በኩል ኳስን ተቆጣጥሮ ለመጫወት ሲፈልጉ በአንድ አጋጣሚ ባኑ ዲያዋራ ከቅጣት ምት አክርሮ መቶ በጎሉ አግዳሚ ልትወጣበት ችላለች :: በተለይም በመጀመሪያው አጋማሽ ላይ በቀኝ መስመር ላይ ይገኝ የነበረው ሳሙኤል ታዬ በጨዋታው ሂደት ላይ ሲባክን ታይቷል ::

የመጀመሪያው አጋማሽም ብዙም ሙከራዎች ሳይታዩበት ሊጠናቀቅ ችሏል ::

በሁለተኛው አጋማሽ በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ የገቡት ሰበታዎች ጨዋታው በተጀመረ በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ባኑ ዲያዋራ ከመስመር ይዞ በመግባት ለመስኡድ አሻግሮለት መስኡድ መሀመድ ለሰበታ ሁለተኛውን ጎል ሊያስቆጥር ችሏል ::

ከጎሉ መቆጠር በኋላ የቀድሞው ክለቡ ላይ ግብ ያስቆጠረው መስኡድ ደስታውን ሳይገልፅ ተስተውሏል ::

ጅማ አባ ጅፋሮች ጎል ካስተናገዱ በኋላ ወደ ሰበታ ከተማ የግብ ክልል በተደጋጋሚ ለመሄድ ቢችሉም ኳስ እና መረብን ማገናኘት ሳይችሉ ቀርተዋል ::

በተለይም ቅጣት ምት አግኝተው መሀመድ ያኩቡ አክርሮ መቶት የግቡ አግዳሚ የመለሰችበት ሙከራ የምታስቆጭ አጋጣሚ ነበረች ::

ከደቂቃዎች በኋላ ጅማ አባ ጅፋር ተደጋጋሚ ሙከራዎቻቸው ፍሬ ሊያፈራላቸው ችሏል ::

በቀኝ መስመር በኩል አመረላ ደልታታ ያሻማውን ኳስ መሀመድ ያኩቡ ከተደጋጋሚ ሙከራዎች በኋላ ጅማዎችን ሊያንሰራሩ የሚችሉበትን ጎል አስቆጥሯል ::

ከጎሉ መቆጠር በኋላ ሰበታዎች ወደ ግብ ለመድረስ ሲሞክሩ መሪነታቸውን ያጠናከሩበትን ጎል በአሊ ባድራ አስቆጥረዋል ::

ጨዋታው በሰበታ የበላይነት ሲጠናቀቅ በደረጃ ሰንጠረዡ ሌሎች ቡድኖች እስኪጫወቱ ድረስ በአምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...