መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ ሰበታ ከተማ ሥስት ተጨዋቾችን ሲያስፈርም አንድ ተጨዋች ለማስፈረም ከጫፍ ደርሷል
ሰበታ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሰበታ ከተማ ሥስት ተጨዋቾችን ሲያስፈርም አንድ ተጨዋች ለማስፈረም ከጫፍ ደርሷል

አጋራ
አጋራ

 

አዲስ አዳጊዎቹ ሰበታ ከተማ መስኡድ መሐመድ፣ሳሙኤል ታዬ ና ደሳለኝ ደባሽን ሲያስፍርሙ ዳዊት እስጢፋኖስን ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል።

አምና ከጅማ አባጅፋር ጋር ያሳለፈው የቀድሞው ኢትዮ -ኤሌክትሪክ፣ኢትዮጵያ ቡና ና ደደቢት አማካይ መስኡድ መሐመድን በማስፍረም የመሃል ክፍላቸውን ማጠናከር ችለዋል።በ2003 ከኢትዮጵያ ቡና ጋር በውበቱ አባተ መሪነት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫን ያነሳው መስኡድ በድጋሚ ከቀድሞ እሰልጣኙ ጋር ሚሰራ ይሆናል።

በተመሳሳይ በ2003 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫን ከቡና ጋር ያነሳው ሳሙኤል ታዬ ከ7 ዓመታት የመከላከያ ቆይታ በኃላ ሰበታን ተቀላቅሏል።ከመስመር በመነሳት በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሚታወቀው ሳሙኤል ታዬ ከቀድሞ አሰልጣኙ ውበቱ አባቱ ጋር በድጋሚ ሚገናኝ ይሆናል።

ሥስተኛው ፈራሚ ባሳለፍነው ዓመት ስሑል ሽረ በፕሪምየር ሊጉ አንዲቆይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተው ደሳለኝ ደባሽን በአንድ ዓመት ውል ማስፈረም ችለዋል።መሃል ሜዳ ላይ እሚጫወተው ደሳለኝ ደባሽ ቋሚ ተሰላፊ ለመሆን ብርቱ ፈተና ሊጠብቀው እንደሚችል ይገመታል።

በተጨማሪ ሰበታዎች ዳዊት እስጢፋኖስን ለማስፈረም ከጫፍ የደረሱ ሲሆን ዝውውሩም በቅርብ ቀናት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...