በጥር የዝውውር መስኮት ደደቢትን ዳግም የተቀላቀለው ሮበን ኦባማ ለክለቡ እንድም ጨዋታ ሳያደርግ ክለቡን ለመልቀቅ ተገዷል ።
ከዚህ ቀደም ለደደቢት መጫወት የቻለው ሮበን ኦባማ ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረበት ጊዜ ያልከፈለው ታክስ ስለነበር፤ውዝፍ የታክስ እዳውን መክፈል እስካልቻለ ድረስ በኢትዮጵያ መጫወት ስለማይችል ወደ ሃገሩ ለመመለስ ተገዷል።
በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥ በሚዘጋው የግማሽ ዓመት የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ላይ ሮበን ኦባማን ጨምሮ 8 አዳዲስ ተጨዋቾችን ያስፈረመው ደደቢት ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ከባድ ፈተና ከፊቱ ይጠብቀዋል።
በዳንኤል ጸሃየ ሚመሩት ደደቢቶች ባሳለፍነው ቅዳሜ ደቡብ ፖሊስን በማሸነፍ ከወራጅነት ለመትረፍ ሚያደርጉትን ጉዞ እንድ ብለው ጀምረዋል።
አስተያየት ይስጡ