መነሻ ገጽ ሪፖርት ሪፖርት | ወልዋሎ አዲግራት በኤፍሬም አሻሞ ብቸኛ ግብ የዓመቱ የመጀመርያ ድሉን አስመዝግቧል
ሪፖርትወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሪፖርት | ወልዋሎ አዲግራት በኤፍሬም አሻሞ ብቸኛ ግብ የዓመቱ የመጀመርያ ድሉን አስመዝግቧል

አጋራ
አጋራ

በትግራይ ስታድየም የተካሄደው የወልዋሎ ዓድግራት ዩኒቨርሲቲ ና የደቡብ ፖሊስ ጨዋታ በኤፍሬም አሻሞ ብቸኛ ግብ በባለ ሜዳዎቹ ወልዋሎ አሸናፊነት ተጠናቋል።

በሁለተኛው ሳምንት መቐለ 70 እንደርታን ከገጠመው ቡድን ለውጦችን ኣርገው ወደ ሜዳ የወረዱት በጸጋይ ኪዳነ ማርያም እሚመሩት ወልዋሎዎች የመጀመርያ አጋማሽ ላይ ብልጫ ወስደው መጫወት ችለዋል።በሁለቱም መስመር በኤፍሬም አሻሞ፣አብዱራህማን ፋሴኒ፣እንየው ካሳሁን ኣማካኝነት የደቡብ ፖሊስ ተከላካይ ክፍልን ሲፈትኑ የነበሩት ወልዋሎዎች በሪችሞንድ ኦዶንግ ብዙ የግብ እድሎችን መፍጠር ችለዋል።

በረከት ይስሃቅን በብቸኛ ኣጥቂነት የተጠቀሙት በዘላለም ሽፋራው ሚመሩት ደቡብ ፖሊሶች ኣብዛኛውን የመጀመርያ 45 በመከላከል ተጠምደው ሲያሳልፋ አልፎ እልፎ በበረከት ይስሃቅ ና በብርሃኑ በቀለ አማካኝነት ሙከራዎችን ማድረግ ችለዋል ።ጨዋታው በተጀመረ በ35ኛው ደቂቃ ከግራ መስመር አፈወርቅ ኃይሉ ሰንጥቆ ያሾለከውን ኳስ ኤፍሬም አሻሞ በጥሩ አጨራረስ ወልዋሎን መሪ ያደረገች ጎል ማስቆጠር ችሏል።

በሁለተኛው አጋማሽ ወልዋሎ ከመጀመርያው አጋማሽ አንጻር ብዙም የግብ እድሎችን መፍጠር ባይችሉም እልፎ አልፎ እድሎችን ሲፈጥሩ ነበር በተለይ ከቀኝ መስመር ሪችሞንድ ኦዶንግ እሻምቶት እብዱራህማን ያባከነው ኳስ እሚጠቀስ አጋጣሚ ነበር። ደቡብ ፓሊሶችም የቀኝ መስመር ተከላካዩን ዘነበ ከድርን በብሩክ ኤልያስ በመቀየር ከመጀመርያው 45 የተሻለ ለመንቀሳቀስ ቢሞክሩም ቡድኑ የሚያጠቃበት መንገድ ተገማች እና ያልተደራጀ መሆኑን ተከትሎ በቀላሉ በወልዋሎ ተከላካይ ክፍል በቁጥጥር ስር ሲውሉ ተስተውሏል ።

ብዙ ሙከራዎች ያልታዩበት ሁለተኛው እጋማሽ ምንም ጎል ሳያስተናግድ ጨዋታው በወልዋሎ ዓድግራት ዩኒቨርሲቲ እሸናፊነት ተጠናቋል።

የአሰልጣኞች ኣስተያየት

ፀጋይ ኪዳነ ማርያም -ወልዋሎ አዲግራት ዮ

“የዛሬ ጨዋታ ከባድ ነበር ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ነጥብ መጣላችን ጥሎ ስለመጣ ጫና ውስጥ ሆነን ስለተጫወትን ብዙ የግብ እድሎችን ማምከን ችለናል፤ተከላካይ ክፍላችንም ጥሩ ነበር። “

ዘላለም ሽፈራው -ደቡብ ፖሊስ

“ጨዋታው በተወሰነ መልኩ ጥሩ ነበር ብንሸነፍም ከሌሎች ጨዋታዎች የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገናል።”ጨዋታው በተወሰነ መልኩ ጥሩ ነበር ብንሸነፍም ከሌሎች ጨዋታዎች የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገናል።በመጀመርያው አጋማሽ በተከላካዮቻችን ላይ ያለ መቀናጀት ችግሮች ነበር በሁለተኛው አጋማሽ ያንን ችግር ቀርፈው ገብተዋል። ሌላው የዛሬ ድክመታችን የማጥቃት ኃይላችን ትንሽ ተገድቦ ነበር። ከዛ ውጭ ጨዋታውን ለመቆጣጠር ጥረት አድርገናል።”

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...