በ 15ኛ ሳምንት የኢትዮጽያ ፕሪሜየር ሊግ ይርጋለም ስታድየም ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል ።
ሲዳማ ቡና ቀድሞ ይጠቀማቸው ከነበረው 3 ተጫዋቾችን ለውጦ ሲገባ የመጀመርያው 45 ይሄ ነው የሚባል ሙከራ ሳይደረግበት ብሎም የጨዋታ ፍሰት ሳይኖረው ያለቀ ሲሆን በ አመዛኙ ሲዳማ ቡና ተጭኖ በመጫወት ጥረት ማድረግ ችሏል።
በጨዋታው ሹክቻና ውጥረት የበዛበትና ጨዋታውን ለመቆጣጠር ለዳኞች አስቸጋሪ የሆነ የመጀመሪያ አጋማሽ ነበር። በ 37ኛ” ድቂቃ የ እንግዳው ቡድን የኤሌክትሪኩ አምበል አዲስ ነጋሽ ከ ዳኛው ጋር ከልክ በላይ በመከራከሩ የ ቢጫ ካርድ ሰለባ ሆኖአል።በዚሁ ጨዋታው የጎላ የጎል ሙከራ ሳይደረግበት ወደ መልበሻ ቤት አምርቷል ።

በ 2ኛው አጋማሽ መጀመሪያ ተሽሎ የ ገባው ሲዳማ ቡና ገና ሁለትኛው 45 እንደተጀመረ በ46ኛ ደቂቃ ላይ የኤሌክትሪክ ተከላካዮችን ስህተት ተጠቅሞ ባዬ ገዛኸኝ ባለ ሜዳው ቡድን መሪ የሚሆንበትን ግብ አስቆጥሮ 1-0 መሪነት እንዲይዙ ሲያስችል። በአንጻሩ ኤሌክትሪኮች ከግቧ መቆጠር በኃላ ወደ ግብ በመጠጋት ሙሉለሙሉ የበላይነትን መውሰድ ችለዋል። በ 70 ኛ ደቂቃ ላይ ተክሉ ተስፋዬን በ ሀይሌ እሸቱ ቀይረው ማስገባት ችለዋል ። ከ ተክሉ መግባት በኅላ በተደጋጋሚ ጫና መፍጠር የቻሉት ኤሌክትርኮ በ 78ኛ ደቂቃ ላይ በተክሉ ተስፋዬ አማካኝነት የ አቻነቱን ግብ ማስቆጠር ችሏል ። ከግቧ መቆጠር በኃላ ውጤቱን ለመቀልበስ መሀመድ አብዱለጢፍን ፣አማሃ በለጠንና አዲሱ ተስፋዬን ቀይረው ቢያስገቡም በውጤቱ ላይ ለውጥ ማምጣት አልቻሉም።ጨዋታው በዚሁ የአቻ 1-1 ውጤት ተጠናቋል።
ከጨዋታው መጠናቀቅ በኃላ የሲዳማ ቡና ደጋፊዎች የስታዲየም በር በመዘጋት ቅሬታቸውን አሰምተዋል። በክለባቸው ውጤት ደስተኛ ያልሆኑት ደጋፊዎች ከተወሰኑ አለመግባባቶች በኃላ ግጭቱ በሰላም በውይይት ተፈቷል።
የአሰልጣኞች አስተያየት
አለማየሁ አባይነህ ~ሲዳማ ቡና
” በጨዋታው በተውሰነ መልኩ ቡድኔ ውስጥ አለመረጋጋት ነበረ። በተወሰኑ ተጫዋቾች ምክንያት ውጤቱን አጥተናል። በቀጣይ ዙር ከ ሜዳችን ውጪም በማሸነፍ ፉክክር ውስጥ እንገባለን ”
አሸናፊ በቀለ ~ኢትዮ-ኤሌክትሪክ
“በተጋድሎም ቢሆን ከ ሜዳችን ውጭ 1 ነጥብ መውሰድ ችለናል ።ለ ቀጣዩ 2ኛ ዙር ጠንክረን እንቀርባለን ።ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ከልጄቼ ጋር እንተጋለን ።”
አስተያየት ይስጡ