በኢትዮጵያ ፕሪሜየር ሊግ 6ኛ ሳምንት ጨዋታ ይርጋለም ላይ ሲዳማ ቡና ወልዲያ ከተማን አስተናግዶ ነጥብ ተጋርቶ ሊወጡ ችለዋል፡፡
ልክ 09:03 ደቂቃ ሲል የጀመረው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በኳስ ቁጥጥሩ እንግዳዎቹ ወልዲያዎች የተሻሉ ነበሩ በ2 ተኛ ደቂቃ ፍፁም ገ/ማርያም ያገኘውን እድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡ በ26ኛ ደቂቃ ኤዶም ከቅርብ ርቀት የመታውን ኳስ የሲዳማው ግብ ጠባቀመ ፍቅሩ ውዴሳ አምክኖበታል፡፡ በተደጋጋሚ ወደ ሲዳማ የግብ ክልል መድረስ ቢችሉም ወልዲያዎች የግብ አድል መፍጠር አልቻሉም፡፡ በአንፃሩ ሲዳማ ቡናዎች የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ላይ ተጭነው በመጫወት ጫና ፈጥረዋል፡፡

ለእረፍት የዳኛ ፊሽካ በሚጠበቅበት ሰዓት አናናን ማይክል ከርቀት አክርሮ የመታው ኳስ መረብ ላይ አርፎ በባለ ሜዳዎቹን መሪነት የመጀመርያው አጋማሽ ተጠናቋል፡፡በሁለተኛው አጋማሽ ሲዳማ ቡና ቶሎቶሎ ወደ ጎል በመድ እና የግብ እድሎችን በመፍጠር የተሻሉ ነበሩ በተለይም ማይክል አናን በግራ መስመር ጥሩ ሲንቀሳቀስ ነበር፡፡ በ63ተኛ ደቂቃ ፍፁም ቅጣት ክልል ውስጥ ዮሐንስ ፍሰሐ ኳስ በእጁ በመንካቱ የተሰጠውን ፍ.ቅ.ም ኤዶም ኮዶዞ አስቆጥሮ ጫዋታው አንድ አቻ ሆኗል፡፡

በ75ተኛው ደቂቃ ላይ ወንድሜነህ አይናለም ከ16.50 ውጪ አክርሮ የመታውን ኳስ የወልዲያው ግብ ጠባቂ አድኖበታል፡፡ 80ኛ ደቂቃ ላይ ባዬገዛህኝ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ሊሰናበት ችሏል፡፡ ሲዳማ ቡና የቁጥር ብልጫ ቢኖርበትም ተጭኖ በመጫወት እድሎችን ፈጥረዋል በተለይም አማሀ በለጠ ያመከናት ኳስ እምታስቆጭ ነበረች፡፡ጫዋታው 1ለ1 በሆነ መልኩ ተጠናቋል፡፡
- ማሰታውቂያ -
የአሰልጣኞች አስተያየት
አሰልጣኝ አለማየው አባይነህ
“በቅጣት,በጉዳት እና ለብሔራዊ ቡድን ተመርጠውብን ከቋሚ አሰላለፍ ያጣናቸው ተጫዋቾች ክፍተት ፈጥሮብናል፡፡ተጫዋቾች ሲሟሉልን ወደ አሸናፊነት እንመጣለን፡፡ ”
አሰልጣኝ ዘማርያም ወ/ጊዮጊስ
” ተጋጣሚያችን ውጤት በማጣት ጫና ውስጥ ስለነበረ ተጭነን በመጫወት ለማሸነፍ ነው የተጫወትነው ሆኖም በተከላካይ መስመር ስህተት ጎል ተቆጥሮብናል፡፡የተጎዱብን ሁለት የተከላካይ አማካይና ለብሔራዊ ቡድን ማስመረጣችን ክፍተት ፈጥሮብናል እንደ አጠቃላይ ውጤቱ ጥሩ ነው ፡፡ ”


