መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና ሪፖርት | ሀዲያ ሆሳዕና በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል።
ሀዲያ ሆሳዕናሪፖርትሲዳማ ቡናየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሪፖርት | ሀዲያ ሆሳዕና በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል።

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 7ኛ ሳምንት ላይ የደረሰ ሲሆን በዚህ ዙርም በውድድር አመቱ ድል ማስመዝገብ ተስኖት የቆየው ሀዲያ ሆሳዕና በሜዳው አቢዮ አርሳሞ ስታዲየም ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤት እየራቀው የመጣውን ሲዳማ ቡናን አስተናግዶ በማሸነፍ በሊጉ የመጀመሪያውን ድል ማስመዝገብ ችሏል።

በመጀመሪያው አጋማሽ ሀዲያ ሆሳዕና ከተጋጣሚው ሲዳማ ቡና በተሻለ ሁኔታ በኳስ ቁጥጥር እና ለጎል የቀረቡ ሙከራዎችን በማድረግ ብልጫ ወስዷል። በተለይም ሱራፌል ዳንኤል ወደ ጎል አክርሮ የመታው ኳስ በሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ መሳይ አያኖ እጅ ላይ አርፋለች ከዚያ በኋላ ሀዲያ ሆሳዕና በደስታ ጊቻሞ እና በይሁን እንደሻው አማካኝነት ያደረጉት የጎል ሙከራ አስደንጋጭ ነበር። ብልጫ ወስደው የተጫወቱት ሀዲያ ሆሳዕናዎች በ37ኛው ደቂቃ ላይ ቢስማርክ አፒያ ከመስመር ያሻገረውን ኳስ ሱራፌል ዳንኤል በግንባሩ በመግጨት በመጀመሪያው አጋማሽ ሀዲያ ሆሳዕና መሪ የሆነበትን ጎል አስቆጥሯል።

ከጎሏ መቆጠር በኋላም ሀዲያ ሆሳዕና ይበልጥ ጫና ፈጥሮ ተጫውቷል።
ከእረፍት መልስ በመሃል ሜዳው ብልጫ ወስደው የተንቀሳቁሱት ሲዳማ ቡናዎች በይበልጥ ጫና ፈጥረው ተጫውተዋል። ባደረጉት የጎል ሙከራም ተቀይሮ የገባው አማኑኤል እንዳለ ከረጅሙ አክርሮ የመታው ኳስ በሀዲያ ሆሳዕና ተጫዋቾች ተነክታ የግብ ጠባቂውን ታሪክ ጌትነት አቅጣጫ በመቀየር 67ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ላይ በማሳረፍ 1-1 መሆን ችለው ነበር ብዙም ሳይቆይ ወደ ሲዳማ ቡና የግብ ክልል በተደጋጋሚ መቅረብ የቻሉት ሀዲያ ሆሳዕናዎች 74ኛው ደቂቃ ላይ ቢስማርክ ኦፖንግ የመታት ኳስ ከመረብ ላይ በማረፍ ሀዲያ ሆሳዕና ውጤቱን ወደ 2- 1 መሪነት መቀየር ችሏል።

ውጤቱን አስጠብቆ ለመውጣት ጥንቃቄ የተሞላበት ጨዋታ የተጫወቱት ሀዲያ ሆሳዕናዎች ትዕግስቱ አበራንና ፍራሆል መንግስቱን ቀይረው በማስገባት ውጤቱን አስጠብቀው ወጥተዋል።
ጨዋታው በሀዲያ ሆሳዕና 2- 1 በሆነ ውጤት የተጠናቀቀ ሲሆን ሀዲያ ሆሳዕና በሜዳው ካደረጋቸው ጨዋታዎች የመጀመሪያውን 3 ነጥብ በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ አምስት ከፍ በማድረግ ተስፋውን አለምልሟል።

ሊጉን ወልዋሎ አ.ዩ. በ14 ነጥቦች ሲመራ መቐለ 70 እ. እና ፋሲል ከተማ በቅደም ተከተል በ13 እና በ12 ነጥቦች 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። የኮከብ ግብ አግቢነቱን ደግሞ የፋሲል ከነማው ሙጂብ ቃሲም በ7 ግቦች ቀዳሚ ሲሆን የባህርዳር ከነማው ፍፁም ዓለሙ በ6 እንዲሁም የመቐለ 70 እ. አማኑኤል ገ/ሚካኤል በ5ግቦች ተከታዩን ደረጃ ይዘዋል።

ፎቶ ምንጭ ሆሳዕና ስፖርት

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...