ከዚህ በፊት አስናቀ ሞገስን፣ ምንተስኖት አሎና ሃብታሙ ገዛኸኝን ያስፈረመው መከላከያ አሁን ደግሞ የቀድሞው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የመብራት ኃይልና የሐዋሳን አማካይ ፍቅረየሱስ ተክለብርሀንን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣በመብራት ኃይልና በሐዋሳ ተጫውቶ ያለፈው ፍቅረየሱስ ጦሩን ለአንድ ዓመት ለማገልገል ፊርማውን አኑሯል።
ትናንት ኢትዮጵያ ቡናን ተቀላቀለ ተብሎ ሃትሪክ ስፖርትን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች የተዘገበው የኃይለየሱስ ድርድር ሳይሳካ ቀርቶ ፍቅረየሱስ መከላከያን ተቀላቅሏል።
አስተያየት ይስጡ