ተጨዋቾቹን በማስፈረም የተጠመደው መከላከያ የክረምቱ 8ኛ ፈራሚያቸውን ከሃዋሳ አድርገዋል።ከሃዋሳ ሁለተኛ ቡድን በውበቱ አባተ መሪነት ወደ ዋናው ቡድን ያደገው ደስታ ዮሐንስ ላለፋት ዓመታት የቡድኑ ወሳኝ ተጨዋች ሆኖ አገልግሏል።
በግራ መስመር ተከላካይነት እንዲሁም በመስመር አጥቂነት ሚጫወተው ደስታ ዮውሃንስ በዘላለም ሽፈራው እየተመራ በክረምቱ ዝውውር በንቃት እየተሳተፈ ሚገኘውን መከላከያን የወቅቱ ስምንተኛ ፈራሚ ሆኖ ተቀላቅሏል።
በኣፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጋናን በገጠመበት ጨዋታ በአብርሃም መብራህቱ ጥሪ ተደርጎለት መጫወት የቻለው ደስታ በሚቀጥሉ ዓመታት በጦሩ ማልያ ምንመለከተው ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ