መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ መቐለ 70 እንደርታ ድሬዳዋ ከተማን በማሸነፍ የ2011 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫን አነሳ
መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

መቐለ 70 እንደርታ ድሬዳዋ ከተማን በማሸነፍ የ2011 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫን አነሳ

አጋራ
አጋራ

 

ከ60 ሺህ በላይ ደጋፊ በትግራይ ስታድየም ታድሞ በተከታተለው የመቐለ 70 እንደርታ ና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ በባለ ሜዳዎቹ ምዓም እንበሳዎች እሸናፊነት ተጠናቋል።

ብዙ ሙከራዎች እና የመቐለ 70 እንደርታ የኳስ ቁጥጥር ና ሙከራ በላይነት በታየበት የመጀመርያው ጥሩ ሚባል ፋክክር አሳይቷል።በ4-2-3-1 የተጨዋቾች እሰላለፍ ወደ ሜዳ የገቡት መቐለዎች ከሁለቱም መስመሮች በሚነሱ ኳሶች እድሎችን ሲፈጥሩ ነበር፤በተለይም ኦሰይ ማውሊ፣ያሬድ ብርሃነ ና እማኑኤል ገብረሚካኤል ያደረግዋቸው ሙከራዎች ሚጠቀሱ ናቸው።እንግዶቹ ድሬዎች እብዛኛው ጊዚያቸውን መሃል ሜዳ ላይ ትኩረት ያደረጉ እጫጭር ና የተቆራረጡ ቅብብሎሽ ከማድረግ ውጪ ይህ ሚባል የግብ ዕድል መፍጠር ተስንዋቸው ታይቷል።መደበኛ የመጀመርያ እጋማሽ ተጠናቆ ዳኛው በጨመሩት 3 የባከኑ ደቂቃዎች ላይ እማኑኤል መትቶት በድሬዳዋ ተከላካዮች በእጅ መመለሱ ተከትሎ የተሰጠውን ፍፁም ቅጣት ምት ጋናዊው ኦሰይ ማውሊ እስቆጥሮ የመጀመርያው እጋማሽ በመቐለ መሪነት እንዲጠናቀቅ እድርጓል።

ሁለተኛው እጋማሽ መቐለዎች ያሬድ ብርሃነን በዮናስ ገረመው በመቀየር የጨዋታ ስልታቸውን ወደ 4-4-2 በመቀየር ተጫውተዋል።ድሬዎች በበኩላቸው መጀመርያ እጋማሽ ላይ የተጠቀሙበት እሰላለፍ ለውጥ ሳያደርጉ ገብተዋል።ጫና መፍጠራቸውን የቀጠሉት መቐለዎች 55ኛው ደቂቃ ላይ ዮናስ ገረመው ከማእዘን ምት ያሻገረውን ኳስ የድሬ ተከላካዮች ኳሱን በሚያወጡበት ጊዜ በእጅ መንካታቸውን ተከትሎ የተሰጠውን ፍፁም ቅጣት ምት እማኑኤል ገብረሚካኤል እስቆጥሮ የመቐለን ጎል ወደ ሁለት ከፍ ማድረግ ችሏል።

ከግቡ መቆጠር በኃላ በተሻለ መልኩ ሙከራዎችን ማድረግ የቻሉት ድሬዎች ከርቀት በሚመቱ ኳሶች እድሎችን መፍጠር ችለዋል፤የዚህም ውጤት በ78ኛው ደቂቃ ላይ ኤልያስ ማሞ የበረኛው ሶፈንያስ ሰይፈ መውጣትን ተምልክቶ ከርቀት የመታው ኳስ ቀጥታ የመቐለ መረብ ላይ ሊያሳርፈው ችሏል።ከግቡ በኃላ መቐለዎች መሪነታቸውን ለማስጠበቅ ያደረጉት ሙከራ ተሳክቶላቸው ጨዋታው 2ለ1 ማሸነፍ ችለዋል።

ሽረ ላይ የሊጉ መሪ ፋሲል ከነማ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ መቐለ 70 እንደርታ የ2011 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮን ሊሆን ችሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...