መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ መቐለ 70 አንደርታ ሥስት ተጨዋቾችን ዝውውር አጠናቀዋል
መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

መቐለ 70 አንደርታ ሥስት ተጨዋቾችን ዝውውር አጠናቀዋል

አጋራ
አጋራ

በመቐለ ከተማ የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን እያከናወኑ ሚገኙት ሻምፒዮኖቹ ናይጀርያዊው ላውረንስ ኤድዋርድ፣አቤል መብራህቱ እና ፍፁም ተክለማርያም አስፈርመዋል።

የተከላካይ መስመር ተጨዋች ለማስፈረም በእንቅስቃሴ ውስጥ የነበሩት መቐለ 70 እንደርታ በመጨረሻም ናይጀርያዊውን ላውረንስ ኤድዋርድን አስፈርመዋል።ከዚህ በፊት በኢራን ሊግ አልሲናትና ካርባያን ክለቦች ተጫውቷል።

ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ብሄራዊ ሊግ ላይ ከትግራይ ውሀ ስራ ጋር ያሳለፈው አቤል መብራህቱ መቐለ 70 እንደርታን መቀላቀል ችሏል።ከዚህ በፊት ለስሑል ሽረ፣መቐለ 70 አንደርታ መጫወት የቻለው አቤል ከብዙ ዓመታት በኃላ ወደ ቀድሞ ክለቡ መመለስ ችሏል።

ላለፋት ሁለት ዓመታት ከዋናው ቡድን ጋር መደበኛ ልምምድ ሲያከናውን የነበረው ፍፁም በቀዋሚነት ክለቡን መቀላቀል ችሏል።በ2010 በዮውሃንስ ሳህለ አማካኝነት 2011 ላይ ከፈረሰው ሁለተኛ ቡድን ወደ ዋናው ቡድን ያደገው ፍፁም መቐለ 70 እንደርታ መሀል ሜዳ ላይ ያላቸውን የተጨዋች አማራጭ ሊያሰፋላቸው እንደሚችል ይገመታል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...