ባልተጠበቀ ዝውውር መቀሌ ጋቶች ፓኖምን በአንድ አመት አስፈረመ፡፡
የፕሮፌሽናል እድል በማግኘቱ ኢትዮጵያ ቡናን ለቆ ወደ ሩሲያው አንዚማካቻካላ ቢያቀናም የተሳካ የውድድር ቆይታን ማሳለፍ ያልቻለው ጋቶች ፓኖም ዳግሞ ዉሉን አቋርጦ ወደ ሀገሩ መምጣቱ ይታወሳል በተደጋጋሚ የቀድሞው ክለቡን ኢትዮጵያ ቡናን ይቀላቀላል ቢባልም በሀገሪቱ ባሉ በርካታ ክለቦች ተደጋጋሚ የማስፈረም ጥያቄን አቅርበውለት በገንዘብ ባለመስማማቱ ወደ ደቡብ አፍሪካውን ቢድወስት ቪትስን ለመቀላቀላቀል በሙከራ ቢየያመራም ከስምምነት ላይ ባለመድረሱ ወደ ሀገር ቤት በመምጣት አስቀድሞ ጥያቄ ላቀረበለት መቐለ ከተማ በአንድ አመት ውል መቀላቀሉ ተሰምቷል፡፡ ክለቡ ተጫዋቹን ለአንድ ዓመት የውድድር ዘመን ወርሀዊ 133,000 ብር ክፍያ እንደሚያገኝ ታውቋል።
በ2002 ከጋምቤላ ክልል በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ አማካኝነት ከ17ዓመት በታች የአፍሪካ ወጣቶች ዋንጫ መጫወት ሲችል በ2003 በአሰልጣኝ ስዩም አባተ አማካኝነት ኢትዮጵያውያ ቡናን መቀላቀሉ እሚታወስ ነው። ጋቶች ከቡና ወጣት ቡድን ወደ ዋናው ቡድን በማደግ አስከ 2009 ኢትዮጵያ ቡናን አገልግሏል።
አስተያየት ይስጡ