መነሻ ገጽ መቐለ ሩጫ በመቐለ ከተማ የ10 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር ተካሄደ
መቐለ ሩጫዜናዎች

በመቐለ ከተማ የ10 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር ተካሄደ

አጋራ
አጋራ

 

በመቐለ ከተማ በሁለቱም ፆታዎች የ10 ኪሎ ሜትር ውድደር ዛሬ ተካሄደ።

ውድድሩ ስፖርት ባህል ያደረገ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ብሎም ክልሉንና አገር ወክለው የሚወዳደሩ አትሌቶች ለማፍራት ዓላማ ያደረገ እንደነበር ተገልጿል።

መነሻውንና መድረሻው ሮማናት አደባባይ ባደረገው  ውድድር ከ9ሺህ የሚበልጡ አትሌቶችና የከተማው ማህበረሰብ ተሳትፏል።

በሁለቱም ፆታ ከአንደኛ አስከ ሶስተኛ ደረጃ ይዘው  ውድድራቸውን ላጠናቀቁ አትሌቶች የገንዘብና የዋንጫ ሽልማት ተሰጥቷል።

በወንዶች በተደረገው ውድድር አንደኛ የወጣው ገብረጅወርግስ ተክላይ 60ሺህ ብር ፤ሁለተኛ የወጣው ምሩፅ ውበት 30ሺህ ብር፤ሶስተኛ ለወጣው ኃይለማርያም ኪሮስ 20ሺህ ብር ተሸልመዋል።

በተመሳሰይ በሴቶች ውድድሩን ያሸነፉት ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ በመውጣት ያሸነፉት ፈትየን ተስፋይ ፣ ጎይቶም ገብረስላሴና አበራሽ ምናሰቦ ሽልማቱን ተቀብለዋል።

ለሶስተኛ ጊዜ በከተማው የተካሄደው ውድድር የተዘጋጀው አትሌት ገብረእግዚብሔር ገብረማርያምና ባለቤቱ ወርቅነሽ ኪዳነ ባቋቋሙት ናትና ስፖርት ኤቨንትስ በተባለ ተቋም ነበር።

ውድድሩን ያስጀመሩት የትግራይ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ገነት አረፈ የማህበረሰቡ ስጋት እየሆኑ የመጡ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመፈወስ ዓይነተኛ መፍትሄ ስፖርት መሆኑ ማወቅና መተግበር አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

Via – Ethiopia news Agency

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...