በማልታ የሴቶች ሱፐር ካፕ ጨዋታ ቢርኪርካራ ምጋር ዩናይትድን አምስት ለ ዜሮ በማሸነፍ የዓመቱ የመጀመርያ ዋንጫቸውን አሳክተዋል።ልማደኛዋ የግብ አዳኝ ሎዛ አበራ በጨዋታው ሁለት ግብ በማስቆጠር ከክለብዋ ጋር የመጀመሪያ ዋንጫዋን ማንሳት ችላለች፤ቀሪ ሥስት የቢርኪርካራ ግቦችን አንማሪ ሰይድ፣ራይና ጉስቲ ና ኬይሊ ዊልስ አስቆጥረዋል።

በሰባት የሊግ ጨዋታዎች 17 ግቦችን ያስቆጠረቸው ሎዛ አበራ የማልታ የሴቶች ፕሪምየር ሊግ ኮኮብ ግብ አግቢነትን እየመራች ትገኛለች።ሎዛ አበራ እስካሁን ባደረገቻቸው የሊጉ ጨዋታ 17 ጎሎች የወዳጅነት ጨዋታ 1ጎል የዛሬውን ሶስት ጎሎች ጨምሮ 21 ጎሎች በስሟ ተመዝግበዋል።
አስተያየት ይስጡ