ትላነት ምሽት በተጠባቂው የማልታ ሊግ ሁለት ግቦችን ያስቆጠረችው ሎዛ አበራ ነገም በወዳጅነት ትጠበቃለች።
ማንም ተከላካይ ሊያቆማት ያልቻለው የጎል አዳኟን ኢትዮጵያዊቷ ሎዛ አበራ በማልታ በተሰለፈችባቸው ጨዋታ ኳስ እና መረብን ሳታገናኝ የወጣችበት የለም። ግብ አግቢነቷን ለማስቀጠል ነገ ክለቧ ቢሪካርካራ በናሽናል ስታዲዮም ባኒክ ኦስትራቫ በወዳጅነት ጨዋታ የሚገጥም ይሆናል፡፡ ከዚህ ቀደም ከቡድኗ ጋር በወዳጅነት ጨዋታ ተሰልፋ 1 ግብ ማስቆጠር ስትችል። ዛሬ የምትሰለፍበት ሁለተኛዋን የወዳጅነት ጨዋታ ደግሞ ግብ እንደምታስቆጥር ይጠበቃል።
አስተያየት ይስጡ