የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አሸናፊዋ ሎዛ አበራ የማልታ ሊግ ሻምፒዮን የሆነውን ቢርኪርካራ በአንድ ዓመት ውል ፈርማለች።
ከስዊድን ያልተሳካ ሙከራ በኃላ በግማሽ ዓመት ለአዳማ ከተማ የፈረመችው ሎዛ ከአዳማ ጋር የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ማንሳት ችላለች።
በሃዋሳ ከተማ የጀመረው የሎዛ የእግር ኳስ ህይወት ደደቢት፣አዳማ አቋርጦ ቢርኪርካራ ላይ ማረፍያውን አድርጓል።
የማልታን ሊግ ለ8 ጊዜ ማንሳት የቻለው ቢርኪርካራ የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ተከትሎ በቀጣይ ዓመት በቻምፒዮንስ ሊግ አውሮፖ ሚሳተፍ ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ