መነሻ ገጽ ዜናዎች ለፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሲሰጥ የነበረው የተጫዋቾች ምዝገባ የመረጃ አያያዝ ስልጠና በትናትናው እለት ተጠናቀቀ፡፡
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ለፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሲሰጥ የነበረው የተጫዋቾች ምዝገባ የመረጃ አያያዝ ስልጠና በትናትናው እለት ተጠናቀቀ፡፡

አጋራ
አጋራ

የአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባዘጋጀው /FIFA Connect Platform/ የመረጃ ቋት ተጫዋቾችንና የክለብ አባላትን መረጃ አያያዝ ስልጠና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ለፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ለሁለት ቀን ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በትናንትናው እለት 05/06/2011 ዓ/ም ተጠናቀቀ፡፡

ለሁሉም ለፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በተዘጋጀው ስልጠና አስራ አንድ ክለቦች የተገኙ ሲሆን በስልጠናው ላይ በአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባዘጋጀው /FIFA Connect Platform/ የመረጃ ቋት አስተማማኝ እና የተሟላ የተጫዋቾች እና የቡድኑ አባላትን ምዝገባ መረጃን መያዝ የሚያስችል ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ይህ ለውጥ የተጫዋቾች ዝውውር ግልፅነት እና ፕሮፌሽናሊዝምን ከመጨመር ባሻገር በተለይ ውጤታማ እና ወጥ የሆነ የተጫዋቾች የልምምድ ካሳ ክፍያ ስርዓት እንዲኖር ያስችላል ፕሮግራምሙም ከሐምሌ 1 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡

በመጨረሻም በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተዘጋጀ ሰርተፊኬት ሥልጠናውን ለተከታተሉ ሰልጣኞች ተበርክቶላቸዋል፡፡

via – EFF

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...