መነሻ ገጽ ዜናዎች ለአንድ ሳምንት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተሰጠው የእግር ኳስ አስልጣኞች አሰልጣኝ ስልጠና ዛሬ ተጠናቀቀ፡፡
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

ለአንድ ሳምንት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተሰጠው የእግር ኳስ አስልጣኞች አሰልጣኝ ስልጠና ዛሬ ተጠናቀቀ፡፡

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቴክኒክ ዲፓርትመንት ከተለያዩ ዩኒቭርስቲዎች ለተውጣጡ 33 የስፖርት ሳይንስ መምህራን ሲሰጥ የነበረው የእግር ኳስ አሰልጠኞች ስልጠና ከ7ቀናት የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ስልጠና በኋላ በዛሬው ዕለት ተጠናቀቀ፡፡
ይህ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አማካኝነት የተሰጠው የሀገር ውስጥ ኢንትራክተሮች ስልጠና አላማ ያደረገው በሚሄዱባቸው የሃገራችን ክፍሎች ለእግር ኳስ አሰልጣኞች ከክልሉ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ስልጠናዎችን እንዲሰጡ ለማደረግ የታቀደ መሆኑን ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቴክኒክ ዳይሬክተር ኢንስትራክተር መኮንን ኩሩ ገልጸውልናል፡፡
ዛሬ በነበረው የመዝጊያ ፕሮግራም የተገኙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ባደረጉት ንግግር በቀጣይ በርካታ ስራዎች ከሰልጣኖቹ እንደሚጠበቅ የገለጹ ሲሆን፤ አክለውም የወደፊቱን የተሻለ ብሔራዊ ቡድን ለማግኘት ሁሉም ለሀገሩ የሚጠበቅበትን እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡


ስልጠናውን የተከታተሉት የዩኒቨርስቲ መምህራንም ይህን ሀላፊነት በሚገባ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ስለመወጣታቸው የቴክኒክ ዳይሮክተሬቱ ክትትል እንደሚያደርግ እና ግንኙነታቸውም በጠበቀ መልኩ እንደሚያስቀጥሉ ኢንሰትራክተር መኮንን ኩሩ ገልጸውልናል፡፡ በስተመጨረሻም ለሰልጣኞቹ የምስክር ወረቀት ተሰጧቸዋል፡፡

Via- Eff website

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...