ዘላለም ሽፈራውን በአሰልጣኝነት የቀጠሩት መከላከያ ሃብታሙ ገዛሀኝን ከሲዳማ ቡና አስፈርመዋል።
ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ሲዳማ ቡና ለዋንጫ ባደረገው ሩጫ ላይ 11 ግቦችን በማስቆጠር ከፍተኛ ድርሻ ያበረከተው ሃብታሙ እንደ አዲስ እየተገነባ ያለውን መከላከያን ተቀላቅሏል።
ጦሮቹ በያዝነው የክረምት ተጨዋቾች መስኮት ዝውውር በንቃት እየተሳተፋ ሲሆን ምንተስኖት አሎ፣ነስረዲን ሃይሉ እና አስናቀ ሞገስን ማስፈረም ችሏል።
አስተያየት ይስጡ