ሀድያ ሆሳዕና ግዙፋን አጥቂ ቢስማርክ አፒያን ለማስፈረም ተስማምቷል።ባሳለፍነው የውድድር አመት የሰርቢያውን ማልዶስት ሊካኒን በመልቀቅ ጅማ አባጅፋርን የተቀላቀለው ቢስማርክ አፒያ ከአባጅፋሮች ጋር ግማሽ የውድድር አመት ካሳለፈ በኃላ ስሁል ሽረን በመቀላቀል ቀሪውን ግማሽ አመት ከስሁላውያን ጋር አሳልፏል።ስሑል ሽረ ከሊጉ አንዳይወርድ ከፍተኛ ድርሻ የነበረውን የአጥቂ ክፍል ከቢስማርክ አፖንግ አና ሳሊፍ ፎፎና ጋር በመሆን የመራው አፒያ በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግም ከአዲስ አዳጊዎቹ ጥሩ ጊዜ ሊያሳልፍ አንደሚችል ይገመታል።
ሀድያ ሆሳዕና ቢስማርክ አፒያን ማስፈረማቸው ተከትሎ የክረምቱ ፈራሚዎቻቸው ቁጥር 12 ማድረስ ችለዋል።


