መነሻ ገጽ ዜናዎች ሀትሪክ 12ኛ ሳምንት ዕይታ ( የተቆጠሩ ግቦች እና የተመዘገቡ ውጤቶች)
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሀትሪክ 12ኛ ሳምንት ዕይታ ( የተቆጠሩ ግቦች እና የተመዘገቡ ውጤቶች)

አጋራ
አጋራ

 

በ12ኛ ሳምንት የተመለከትናቸውን ዋና ነጥቦች አንስተናል።

የተቆጠሩ ግቦች

የ12ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ትላንት እና ዛሬ በደረጉ ጨዋታዎች ፍፃሜውን ሲያገኝ። በዚህ ሳምንት በጠቅላላ 24 ግቦች ተቆጥረዋል ይህ ማለት ደግሞ ባለፈው ሳምንት ከተቆጠሩ ግቦች በ8 ከፍ ብሏል። ሊጉ ከተጀመረ 24 ግቦች ሲቆጠሩ ይህ ለመጀመሪያ ግዜ ነው። 20 ተጫዋቾች ግብ ሲያስቆጥሩ 16ቱ ግቦች በተለያዩ ተጫዋቾች የተቆጠረ ሲሆን እዮብ አለማየሁ ፣አህመድ ሁሴን፣አቤል ያለው እና ጌታነህ ከበደ ሁለት ሁለት ግቦችን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። የሳምንቱ ፈጣን ግብ ያስቆጠረው እዮብ አለማየሁ በ48ኛው ሰከንድ ሲሆን ፍፁም ገብረማርያም እና ሳሊፍ ፎፋና 81ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠሯቸው ግቦች በሳምንቱ ዘግይተው የተቆጠሩ ግቦች ናቸው። ሁለት ግቦች በፍፁም ቅጣት ምት አንድ ግብ ላይ ደግሞ በራስ መረብ ሲቆጠሩ። ሶስት ግቦች ደግሞ በውጭ ተጫዋቾች መቆጠር የተቆጠሩ ሆነው አልፈዋል።

 

የተመዘገቡ ውጤቶች

በዚህ ሳምንት የተደረጉ ሁሉም ጨዋታዎች በባለሜዳዎቹ አሸናፊነት መጠናቀቅ የቻለ ሲሆን። ስድስቱ ከሜዳቸው ውጭ የተጫወቱ ቡድኖች የተቃራኒ መረብ ላይ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል። በአንድ ጨዋታ ማለትም የቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ እና ሲዳማ ቡና በጠቅላላ 8 ግቦች የታዩበት ጨዋታ ሆኖ ሲያልፍ። ሶስት ቡድኖች ደግሞ በተመሳሳይ 3-0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ሁለት ቡድኖች ብቻ አንድ ግብ ብቻ አስቆጥረው ሶስት ነጥብ ይዘው መውጣት ችለዋል። ወልቂጤ ከተማ ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን ሲያስመዘግብ ኢትዮጵያ ቡና እና ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ ለተከታታይ ሁለተኛ ግዜ ሸንፈትን አሰተናግዷል። ሀድያ ሆሳዕና አሁንም ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ተቸግሯል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...