ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ
ተወዳጇ ጋዜጣ ሀትሪክ ስፖርት ነገም የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛሎት ከተፍ ትላለች።
ሀትሪክ በሀገር ውስጥ መረጃዋ THE BIG iNTERVIEW በሚለው አምድ የኢትዮጵያ ቡናውን እንዳለ ደባልቄ ካክሽን ይዛሎት ቀርባለች። ተጨዋቹ ምን ብሎ ይሆን? ሀትሪክ ከዛ ውጪም በፕሪምየር ሊግ የውድድር ጅማሬዎች ለሲዳማ ቡና ጎሎችን እያስቆጠረ ከሚገኘው ስኬታማው አጥቂ አዲስ ግደይ ጋር ቡድናቸው እያስመዘገበው ስላለው ውጤት እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ቆይታን አድርጋ ተጨዋቹ ምላሹን ሰጥቷታል።
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዋም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግን አስመልክቶ ተጠባቂ ስለነበረው የማንቸስተር ሲቲና የአርሰናል ጨዋታ እንደዚሁም ደግሞ ስለ ሊጉ መሪ ሊቨርፑል አልሸነፍ ባይነት እና ሌሎችንም መረጃዎች ይዛሎት ቀርባለች።
ሀትሪክ አታምልጦት።
አስተያየት ይስጡ