ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ
ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ ማክሰኞ እናንተን ልታገኝ ዝግጅቷን አጠናቃለች፤ ለመሆኑ ሀትሪክ በነገው እትሟ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ በመውጣት ለእናንተ ውድ አንባቢዎቿ ታስነብብ ይሆን?
የሀገር ውስጥ ዓምዷ ላይ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት THE BIG INTERVIEW ገፅ ላይ የጋዜጣው ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተር ጋዜጠኛ ይስሃቅ በላይ የቀድሞውን የኪቤአድ አሰልጣኝ አቶ አስናቀ ደምሴን በማቅረብ ሊወዱት የሚችሉትን ቃለ-ምልልስ አድርጎላችዋል፤ አቶ አስናቀ ምን ብለው ይሆን?
ሀትሪክ ከዛ ውጪም በፕሪምየር ሊጉ የዘንድሮ የውድድር ዘመን ተሳትፎ ዙሪያ የክላባቸው ተሳትፎ እና በራሱ የኳስ ሕይወት ዙሪያም ከመቐለ 70 እንደርታው ጠንካራ የተከላካይ ስፍራው ተጨዋች አሚን ነስሩም ጋር ሀትሪክ ቆይታ አላት፤ ተጨዋቾቹ ምን ብለው ይሆን?
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዎቿም ነገና ረቡዕ በሚካሄዱት ወሳኝ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችና በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናቶችም ስለተካሄዱት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ እና የሌሎች የአውሮፓ ሊግ ጨዋታዎች ዙሪያም ሲያነቡት ሊወዱት የሚችሉትን ዘገባ ይዛሎት ቀርባለች፡፡
ሀትሪክ የእናንተው ናት አታምልጦት፡፡
ሀትሪክን ከሳምንታዊ ጋዜጣዋ በተጨማሪ http://www.hatricksport.com/ ድረ-ገፃችን ላይ አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉና አሁኑኑ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፤ የሀትሪክ ቤተሰብም ይሁኑ፡፡
የሀትሪክ ጋዜጣ የነገው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል፡፡
አስተያየት ይስጡ