መነሻ ገጽ ዋልያዎቹ “በሜዳችንና በደጋፊያችን ፊት እንድንጫወት የሚቻለውን ሁሉ ጥረት እንዲደረግ ማስቻል ቀጣይ የቤት ስራ እንደሆነ መጠቆም እወዳሃለው” አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

“በሜዳችንና በደጋፊያችን ፊት እንድንጫወት የሚቻለውን ሁሉ ጥረት እንዲደረግ ማስቻል ቀጣይ የቤት ስራ እንደሆነ መጠቆም እወዳሃለው” አሰልጣኝ ውበቱ አባተ

አጋራ
አጋራ

በደቡብ ሱዳኑ ጃሙስ ክለብ የሚገኙት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከዛሬው የዋልያዎቹ ድል በኋላ ሁለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

“በቅድመ ማጣሪያ ጨዋታችን ሳኦቶሜ እና ፕሪንስፔን አራት ለዜሮ በሆነ ድምር ውጤት በማሸነፍ ወደ ምድብ ድልድል በመግባታችን ደስ ብሎኛል።ይህንን ድል ላሳኩት የቡድን አባላትም እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ።

በሌላ በኩል በግሌ ስለ ብሔራዊ ቡድናችን ከታች ባሉት ነጥቦች ላይ አስተያየት መስጠት እፈልጋለሁ።

1ኛ ከአምስት አመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሜዳችን በተመልካች ፊት እንድንጫወት ከፍተኛ ስራ በመስራት ቡድናችን ወደ ሀገር ቤት እንዲመለስ ሁኔታዎችን ያመቻቹትን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድርን ከልቤ እያመሰገንኩ በቀጣይ የሚኖሩ የብሄራዊ ቡድን ጨዋታዎችንም በሜዳችንና በደጋፊያችን ፊት እንድንጫወት የሚቻለውን ሁሉ ጥረት እንዲደረግ ማስቻል ቀጣይ የቤት ስራ እንደሆነ መጠቆም እወዳለው። ብሔራዊ ቡድናችን በሜዳው ቢጫወት የሚያገኘው በርካታ advantage እንዳለ ሆኖ ይህን ዕድል አሳልፈን መስጠት ተፅኖው ከፍተኛ እንደሆነ መገንዘብ ይገባል። ቡደናችን ለሚያስመዘግበው ውጤትም አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል።

2ኛ ምንም እንኳን በዚህ ቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ተጋጣሚያችንን አሸንፈን ብናልፍም ብሔራዊ ቡድናችን በየትኛውም መመዘኛ በዚህ ደረጃ መገኘት አና ከመሰል ሀገራት ጋር መወዳደር መመልከት የማይገባን የማይመጥነን በመሆኑ በቀጣይ በሚደረጉ የምድብ ጨዋታዎች ላይ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ሀገራችንና ቡድናችንን በሚመጥን ደረጃ ላይ ማስቀመጥ እንደሚጠበቅብን በማመን ሁላችንም የበኩላችንን ድጋፍ በማድረግ ከብሔራዊ ቡድናችን ወደዚህ አዘቅት እንዳይመለስ ለማድረግ ከብሔራዊ ቡድኑ ጎን እንድንሆን ማሳሰብ እወዳለሁ።” በማለት አሰልጣኙ ገልፀዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...