በጉባኤው ላይ ያለፈው አመት አፈፃፀምና የአዲሱ አመት ዕቅድ ይፋ ተደርገው በክልሉ እግርኳሳዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ነጥቦችን በማንሳት ከክልሉ የተወጣጡ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ምክክር ተደርጓል። የውይይቱን መድረክ ሲመሩ የነበሩ የክልሉ እግርኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊ የነበሩ አቶ ፍሮምሳ ለገሰና የፌዴረሽኑ ፕሬዘደንት አቶ ሙስጠፋ ከድር በጉባኤው ላይ ከታደሙት አካላት ጋር የተለያዩ ነጥቦችን አንስተው አወያይተዋል።
በጉባኤው ላይ የክልሉ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትና አዳዲስ ስራ አስፈፃሚዎችና በመሆን ለቀጣዮቹ አራት አመታት እንዲያገለግሉ በአስመራጭ ኮሚቴ የቀረቡት 7 አባላት ያላቸው ግለሰቦች የነበሩ ሲሆን። ከ21 የክልሉ ዞኖች፣ ከ19 ከተማ አስተዳደር እንዲሁም ከ2 የአሰልጣኞች ማህበራትና ከ2 የአርብትሮች ማህበራት ባጠቃላይ በ40 ድምፅ ሰጪዎች ምርጫው ተከናውነዋል።
ለምርጫው የቀረቡ እጩዎች
- ማሰታውቂያ -
ዶር ዋቅጅራ ስማ (ቢሾፍቱ ከተማን በመወከል)
ወ/ሮ አበራሽ ታደሰ (ቢሾፍቱ ከተማን በመወከል)
አቶ ደረጄ ሙላቱ (ነቀምቴ ከተማን በመወከል)
አቶ ግርማ በቀለ (የሰሜን ሸዋ ዞንን በመወከል)
አቶ ድንቁ አበበ (ለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ከተማን በመወከል)
አቶ ከበደ ወርቁ ሰበታ ከተማን በመወከል እንድሁም
ዶር እንደገናለም አዋስ አዳማ ከተማን በመወከል ቀርበው የነበረ ሲሆን ዶር ዋቅጅራ ስማ ለቀጣዮቹ 4 አመታት የኦሮሚያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕረዚዳንት በመሆን ወ/ሮ አበራሽ ታደሰ ደግሞ ፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን እንዲያገለግሉ በጉባኤው ሙሉ ድምፅ ሲመረጡ የተቀሩት እጩዎች የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በመሆን እንዲያገለገሉ ተመርጧል።
የምርጫ ስነስርዓቱ ከተከናወነ በኋላም የቃለመሀላ ስነስርዓት በማከናወን ከቀድሞው የፌዴሬሽኑ አመራር ጋር የሰነድ ርክክብ በማድረግ አጠናቋል።