በጀርመኑ ኮሎኝ የሚገኘው እና በቀጣዩ ክረምት ወደ ዋናው ቡድን የሚያድገው ወጣቱ የግራ መስመር አጥቂ ተጫዋች ማነው ?
የሚገኘው በጀርመን ከተማ ሲሆን አባቱ ኢትዮጵያዊ ናቸው። “የኢትዮጵያን ታሪክ አብዝቼ እየሰማሁ ስላደኩኝ እግር ኳስ ተጫዋች መሆኔን ሳውቅ ብጫወትላት ደስ የሚል ስሜት ውስጤ ላይ አለ” ይላል ይህንንም ያለው የ17 አመቱ ከጀርመኗ ኮሎኝ ከተማ የተገኘው የግራ መስመር ተጫዋቹ ጆሲሳ ስምዖን ነው።

በጀርመኑ ኮሎኝ ክለብ ውስጥ ከ8 አመቱ ጀምሮ መነሻውን ያደረገው እና በጀርመን ከ17 አመት በታች DFB ፣ በጀርመን LIga A ከ17 አመት በታች እና በUnder championship ከ17 አመት በታች እና በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በDFB ከ19 አመት በታች ቡድን ውስጥ እየተጫወተ የሚገኘው ሲሆን በቀጣዩ ክረምት በጀርመን ቡንደስሊጋ እየተሳተፈ ዘንድሮ 15ኛ ደረጃ ላይ ወደ ተቀመጠው ዋናው የኮሎኝ ቡድን ከሚያድጉ ተጫዋቾች መካከል አንዱ እንደሆነ እየተነገረ የሚገኘው ይህ ወጣት ተጫዋች ኢትዮጵያን ባገለግል እጅ ደስ ይለኛል ሲልም ተናግሯል።
አስተያየት ይስጡ